ለእጩ ተመራቂ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ሊሰጥ ነው
ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ ፉአድ ኢብራሂም እንደተናገሩት የትምህርተ ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደርገው ጥረት የመምህራን የሞያ ብቃት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡
ምዘናው እጩ ተመራቂዎቹ ወደ ስራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት እንዲሰጥ መደረጉ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተዘረጋውን ፓኬጅ ውጤታማ በማድረግ ረገድ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡
በስራ ላይ ያሉት ነባር መምህራንም ምዘናውን እንዲወስዱ በማድረግ ወደሚፈለገው ደረጃ ለማምጣት ተከታታይ የሞያ ስልጠና ይሰጣል ማለታቸውን የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው፡፡
Comments
Post a Comment