የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንደገና ሊቋቋም ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ኤጀንሲ በሚኒስቴር መስሪያ ቤት ደረጃ እንደገና ሊቋቋም ነው። የኤጀንሲው በአዲስ መልክ  መቋቋም ተልዕኮውን በላቀ ብቃት ለመወጣት ያስችለዋል የተባለ ሲሆን ተቋሙ  ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ነው ፥የሚመራውም በጠቅላይ ሚንስትሩ  በሚሾም ዳይሬክተር ጄኔራል   ይሆናል።
ጥራት ያለው መረጃና አስተማማኝ የደህንነት አገልግሎት በመስጠት የአገሪቱን ደህንነት የመጠበቅ ሃላፊነት ለዚህ ተቋም ተሰቶታል፡፡ በአገር ውስጥና በውጭ ሃገር የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ስራን በሃላፊነት በመምራት፤አስፈላጊ ሁኖ ከተገኘ ከውጭ ሃገር አቻ ተቋማት ጋር በትብብር መስራትና በጋራ ኦፕሬሽን ማካሄድም ለዚህ ተቋም ከተሰጡት ስልጣንና ተግባር ውስጥ ተጠቃሾች ናቸው።
በአገሪቱ የኢኮኖሚ፣ እድገትና የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ሊቃጡ የሚችሉ ጥቃቶችንና የመልካም አስተዳደር አሻጥሮችን ተከታትሎ መረጃና ማስረጃ በማስባሰብ ለሚመለከታቸው አካላት እንዲያቀርብም አዲስ የሚቋቋመው ተቋም በአዋጁ ሃላፊነት ተጥሎበታል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ መስሪያ ቤቱን በሚኒስቴር መስሪያ ቤት ደረጃ ለማቋቋም የተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ ተመልክቶ ለዝርዝር እይታ ወደ ሚመለከታቸው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች መርቶታል።
መስሪያ ቤቱ እንደገና እንዲቋቋም መደረጉም በሁሉም የምክር ቤቱ አባላት ዘንድ ድጋፍ  አግኝቷል ። ከዚህ በተጨማሪ በአዋጁ መሰረት የመረጃና የደህንነት ሙያ የስልጠናና የምርምር ተቋምም የሚቋቋም ይሆናል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር