ብሄራዊ የ10ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ነገ ይጀመራል_ መልካም እድል ለሲዴ ልጆች

አዲስአበባ፣ ግንቦት 20፣ 2005(ኤፍ ቢ ሲ) ሀገር አቀፍ የትምህርትምዝና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ደግሞ አጠቃላይ ዝግጅቴን አጠናቅቄለው ብሏል።
ኤጀንሲው ለፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳለው ነገ በሚጀመረው ፈተና 785 ሺ 183 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
ከዚህ ውስጥም 349 ሺ የሚሆኑት  ሴቶች ናቸው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ 1ሺ 347 የመፈተኛ ጣቢያዎች  ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ከ29ሺ 800 በላይ የፈተና ጣቢያ ሀላፊዎች፣ ሱፐር ቫይዘሮች እና ፈታኞች መዘጋጀታቸው ተግልጿ።
በዘንድሮ ሀገር አቀፍ ፈተና በተለየ ሁኔታ ኩረጃን ለመከላከል ሲባል ተንቀሳቃሽ ስልኮችን  ወደ መፈተኛ ጣቢያ ይዞ መምጣት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን ኤጀንሲው አሳስቧል።
ይህን በሚያደርጉ  ተማሪዎች ላይ ከፈተና እስከ መሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ታውቋል።
በሌላ በኩል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከግንቦተ 26 እስከ 29 ድረስ ይሰጣል።
ለዚህ ምዘናም ከ171ሺ 300 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር