በኢትዮጵያ የጤና ትብብር ስትራቴጂ ይፋ ሆነ


የአለም የጤና ድርጅት በኢትዮጵያ ለ4 አመታት የሚቆይ ሀገር አቀፍ የጤና ትብብር ስትራቴጂ ይፋ አደረገ፡፡
ስትራቴጁ  የጤና አገልግሎት ማሻሻል፣ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን፣ የእናቶችና ህፃናት ሞት መቀነስ፣ የስነተዋልዶ ጤናን ማሻሻል እንዲሁም የተደራጀ መረጃን ማሳደግ ትኩረት ያደርጋል፡፡
የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ እንዳሉት ትብብሩ ሀገሪቱ ከቀረፀችው የጤና ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣም በመሆኑ የምእተ አመቱን ግብ ለማሳካት ከፈተኛ ፋይዳ አለው፡፡
ይህም የጤና ልማት ሰራዊትን በማደራጀት በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል ያስችላል ብለዋል፡፡
በአለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ዶክተር ሊዊስ ሳምቦ በበኩላቸው በሀገሪቱ በጤናው ዘርፍ የሚከናወኑ ስራዎችን ከዳር ለማድረስ ድርጅቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር