በኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና ሃዋሳ ከነማ ተጋጣሚዎቻቸውን ኣሸነፉ

አዳማ ላይ እየተካሄደ ያለው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ በደማቅ ሁኔታ በብርቱ ፉክክር ታጅቦ መከናወኑን ቀጥሎ መጋቢት 29/2005 ሶስት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡
በውድድሩ ስኬታማ ይሆናሉ ተብለው ቀዳሚ ግምት ከተሰጣቸው መሐል አንዱ የሆነው መከላከያ በሲዳማ ቡና ሳይጠበቅ 3ለ1 ተሸንፏል፡፡ ትብለጥ ሁለቱን ተራማጅ ቀሪዋን ጎል ለሲዳማ ቡና አስቆጥረዋል፡፡

የአዲስ አበባዎቹ ደደቢትና መድህን ባደረጉት ጨዋታም ደደቢት 3ለ0 አሸንፏል፡፡ ሰናይት ባሩዳ ሁለቱን ብርቱካን ገ/ክርስቶስ ደግሞ አንዷን ጎል ከመረብ አገናኝተዋል፡፡
በሌላው ጨዋታ ሐዋሳ ከነማ ድሬዳዋ ከነማን 3ለ1 ረቷል፡፡ እስከዳር አብዲ፣ ሮዛ ከድርና ዝናሽ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡
የፕሪሚየር ሊጉ መርሃ ግብር ሐሙስ ሲቀጥል ጠዋት 3፡00 ሰዓት አዳማ ከነማ ከሲዳማ ቡና ከሰዓት 10፡00 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመከላከያ ይጫወታሉ፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር