በሴቶች ፕሪምየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ድል ቀናቸው


በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሴቶች ውድድር የምደቡ የመጨረሻ ጨዋታ ሚያዝያ 7/2005 በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ተካሂዷል፡፡
በጨዋታው ሽታየ ሲሳይ 4 ጎል አስመዝግባለች ዘንድሮ በፕሪምየር ሊጉ ያገባችው ጎል 25 በማድረስ መሪነቷን አጠናክራ ቀጥላለች፡፡ አዳማ ከነማ መከላከያን 2 ለ 1 ቢያሸነፍም በግብ ተበልጦ ግማሽ ፍፃሜወን ሳይቀላቀል ቀርቷል፡፡ ከምድቡ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ኃላፊ ሆነዋል፡፡
ኃላፊው ክለብ ቀድሞ የተለየበት የምድብ 2 ጨዋታ ደግሞ 8 ሰዓት ላይ እና 12 ሰዓት ላይ ተካሂዷል፡፡
መውደቃቸውን ያረጋገጡት የመድህንና የድሬዳዋ ጨዋታ በመድህን 4 ለ 3 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
በደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ መካከል የተካሄደው ጨዋታ ደግሞ ደደቢት 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ልዩነት አሸንፏል፡፡ ደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል፡፡
በግማሽ ፍፃሜው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሃዋሳ ከነማ፣ ደደቢት ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር