በሴቶች ፕሪምየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ድል ቀናቸው
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሴቶች ውድድር የምደቡ የመጨረሻ ጨዋታ ሚያዝያ 7/2005 በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ተካሂዷል፡፡
በጨዋታው ሽታየ ሲሳይ 4 ጎል አስመዝግባለች ዘንድሮ በፕሪምየር ሊጉ ያገባችው ጎል 25 በማድረስ መሪነቷን አጠናክራ ቀጥላለች፡፡ አዳማ ከነማ መከላከያን 2 ለ 1 ቢያሸነፍም በግብ ተበልጦ ግማሽ ፍፃሜወን ሳይቀላቀል ቀርቷል፡፡ ከምድቡ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ኃላፊ ሆነዋል፡፡
ኃላፊው ክለብ ቀድሞ የተለየበት የምድብ 2 ጨዋታ ደግሞ 8 ሰዓት ላይ እና 12 ሰዓት ላይ ተካሂዷል፡፡
መውደቃቸውን ያረጋገጡት የመድህንና የድሬዳዋ ጨዋታ በመድህን 4 ለ 3 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
በደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ መካከል የተካሄደው ጨዋታ ደግሞ ደደቢት 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ልዩነት አሸንፏል፡፡ ደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል፡፡
በግማሽ ፍፃሜው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሃዋሳ ከነማ፣ ደደቢት ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ፡፡
Comments
Post a Comment