የሲዳማና የምዕራብ አርሲ አጎራባች ነዋሪዎች የጋራ ተጠቃሚነት ለማጎልበት እየተሰራ ነው
በአሁኑ ወቅት በሀዋሳ ከተማ የተዘጋጀው ስልጠናም የዚሁ ጥረታቸው አንዱ አካል መሆኑን ጠቁመው የህዝብ ለህዝብ ትስስርና መልካም ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ ትኩረት ሰጥተው በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የደቡብ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አርኮ ደምሴ በበኩላቸው ልማትና መልካም አስተዳደር ለማስፈን በተለይ በአጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ችግራቸውን በመግባባት ፈተው የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚደርጉትን ጥረት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ ሁለቱ ክልሎች በጋራ ባዘጋጁት ስልጠና ላይ ከሲዳማና ከምዕራብ አርሲ ዞኖች ከሚገኙ ሰባት አጎራባች ወረዳዎች የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶችና ሴቶችን ጨምሮ 150 የማህበረሰብ ተወካዮች መሳተፋቸውንም አቶ አርኮ አመልክተዋል፡፡ ለሶስት ቀናት በሚካሄደው ስልጠና ላይ በግጭት አፈታትና በሰላም ባህል ግንባታ ከአሁን ቀደም በተከናወኑ በርካታ ተግባራት ላይ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችና ልምድ በመለዋወጥ ተመልሰው ለወከላቸው ህዝብ በማድረስ የጋራ ተጠቃሚታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የሚስችላቸው ትምህርት እንደሚሰጣቸው ታውቋል፡፡
Comments
Post a Comment