በሲዳማ ዞንና ሃዋሳ ከተማ ከ955 ሺህ በላይ መራጮች ተመዘገቡ


ሃዋሳ ጥር 20/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞንና በሃዋሳ ከተማ በመጪው ሚያዝያ ለሚደረገው የአካባቢ ምርጫ ከ955 ሺህ በላይ መራጮች ተመዘገቡ፡፡ የሲዳማ ዞን ምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ዱካሞ እንደገለጹት በዞኑ በሚገኙ 21 ወረዳዎችና በሃዋሳና ይርጋለም የከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ 1 ሺህ 648 የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ ያለምንም ችግር በመከናወን ላይ ነው። እስከ ጥር 21 ድረስ በሚቆየው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ከ1 ሚሊዮን 282 ሺህ በላይ መራጮች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። ከታህሳስ 22 ጀምሮ በመከናወን ላይ ባለው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ለመራጭነት ከተመዘገቡት መካከል 446 ሺህ 699 ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል። በመጪው ሚያዝያ ወር በሚደረገው የአካባቢና የማሟያ ምርጫ ላይ በመራጭነት ለመሳተፍ የመራጮች ምዝገባ በመጪው ማክሰኞ ከመጠናቀቁ በፊት ህብረተሰቡ በመመዝገብ የመራጭነት ማረጋገጫ ካርዱን መያዝ እንዳለበት አስተባባሪው አሳስበዋል። በሃዋሳ ከተማ ሚሊኒየም ቀበሌና ዋጋኔ ዋጮ ቀበሌ ለመራጭነት በመመዝገብ ላይ ከሚገኙት መካከል ወይዘሮ በላይነሽ ደምሴና አቶ ታከለ ተሾመ በሰጡት አስተያየት ያገኙትን ዲሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም የተሻለ ለውጥ በማምጣት ይሰራልናል ብለው ያመኑትን ዕጩ ለመምረጥ የመራጭነት ማረጋገጫ ካርድ ወስደዋል።
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=4931&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር