ደኢህዴን በሲዳማ ዞንና በከተሞች የሚወዳደሩ ከ115ሺህ በላይ እጩዎችን ስያስመዘግብ ሲኣን ግን እስከኣሁን እጩ ኣላስመዘገበም ተባለ


ሀዋሳ ጥር 20/2005 ሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በሲዳማ ዞንና በሌሎች ከተሞች በመጪው ሚያዝያ ለሚካሄደዉ የአካባቢ ምርጫ ደኢህዴን ከ115 ሺህ በላይ እጩዎችን ማስመዝገቡን የዞኑ ምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በዞኑና በከተሞቹ ለሚካሄደዉ ምርጫ ከ1ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውም ተገልጧል ። የጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ዱካሞ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ደኢህዴን ያስመዘገባቸው 115 ሺህ 368 ዕጩዎች ለዞን ፣ለወረዳ ፣ለከተማና ለቀበሌ ምክር ቤቶች ድርጅቱን ወክለው የሚወዳደሩ ናቸው። ደኢህዴን ለሲዳማ ዞን ፣ለሀዋሳ ፣ለይርጋለምና ለአለታ ወንዶ ከተሞች አስተዳደሮችና ለ21 ወረዳዎች ካስመዘገባቸው ዕጩዎች ውስጥ 105 ለዞን ምክር ቤት፣ 277 ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት፣ 1ሺ524 ለወረዳና ፣113 ሺህ 462 ለቀበሌ ምክር ቤት የሚወዳደሩ መሆኑን ተናግረዋል። ለምርጫው በዞኑና በከተማ አስተዳደሮች ፣በወረዳዎችና በቀበሌ ለመወዳደር ካስመዘገባቸው ዕጩዎች ውስጥ 53 ሺህ 289 ሴቶች ሲሆኑ ከነዚህ ዕጩዎች 38 ለዞን ምክር ቤት ፣110 ለከተማ ምክር ቤት፣ 484 ለወረዳ የሚወዳደሩ ሲሆን ቀሪዎቹ ለቀበሌ ምክር ምክር ቤት እንደሚወዳደሩ አስረድተዋል። በዞኑ ለመወዳደር ተመዝግበዉ የመለያ ምልክት ከወሰዱ አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ደኢህዴን፣ ፣ሲአን፣ኢዴአፓና ኢራፓ ውስጥ እስካሁን ዕጩዎቹን ያስመዘገበው ደኢህዴን ብቻ መሆኑን አስተባበሪዉ አመልከተዉ የዕጩዎች ምዝገባ የሚጠናቀቀው በነገዉ እለት በመሆኑ ፓርቲዎቹ ዕጩዎቻቸውን እንዲያስመዘግቡ አሳስበዋል። በተጨማሪም በዞኑ በተቋቋሙ 1648 የምርጫ ጣቢያዎች እስካለፈው አርብ ድረስ 1 ሚሊዮን 33 ሺህ መራጮች መመዝገባቸውንና ከነዚህ ውስጥ 472 ሺህ 764 ሴቶች መሆናቸውን አቶ ብርሃኑ አስታውቀዋል።
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=4932&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር