Posts

Showing posts from December, 2012

ለክብራን የሲዳማወራንቻ ብሎግ ኣንባቢያን በሙሉ

Image
ክብራን የሲዳማወራንቻ ብሎግ ኣንባቢያን ለኣንድ ወር ያህል ስራ ያቆምን መሆናችንን እና ከኣንድ ወር በኃላ በኣዳዲስ ዝግጅቶች የምንመለስ መሆናችንን እናስታውቃለን። እናመሰግናለን መልካም የገና በዓል !

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ (ሲኣን) ኣዲሱ ኣመራር የሲኣንን የቀድሞ ዝና ለመመለስ እና የሲዳማ ህዝብ ፖለቲካዊ መብት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ እንደምታገል ኣስታወቀ ፤ በቅርቡ ለምካሄደው የኣከባቢ ምርጫ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው።

Image
የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ (ሲኣን) ኣዲሱ ኣመራር የሲኣንን የቀድሞ ዝና ለመመለስ እና የሲዳማ ህዝብ ፖለቲካዊ መብት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ እንደምታገል ኣስታወቀ ፤ በቅርቡ ለምካሄደው የኣከባቢ ምርጫ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው። ዝርዝሩን በምከተለው ሊንክ ያዳምጡ:: ለድምጽ ጥራት ማነስ ይቅርታ እንጠይቃለን!   ሲዳማ ተናገር የሬዲዮ ፕሮግራም

የሲዳማ ወጣቶች ንቅናቄ መግለጫ

Statement to Sidama youth movement On 2009, as we all know, the children of Sidama massacred by the current prime Minister of Ethiopia Haile Mariam Desalgn, at Awassa, Loque vicinity, Sidama state and the whole sidama population response to a massacre unprecedented in its nature and scale. On the occasion of the tenth anniversary of that uprising, the youth and students, the children, parents, teachers and other professionals; the workers in town, in commerce, industry and the farms; the religious community - in fact, the entire oppressed population together bound together by the blood that covered the streets of Awassa, the blood that has since soaked the soil of our motherland in even bigger quantities. On this truly historic occasion the nation will pay fitting tribute to the young heroes and martyrs. And so the repression we experience today is not new. But as we can see today the sacrifices of those heroes and martyrs were not in vain. The declaration of eviction of Sid

በሴቶች የፕሪምየር ሊግ ውድድር ሲዳማ ቡና ሩብ ፍፃሜ ገባ

Image
ሰኞ, 24 ታህሳስ 2012 11:05 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ የሴቶች ውድድር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ደደቢትና ሲዳማ ቡና ከየምድባቸው በበላይነት አጠናቀዋል። የምስራቅ ዞን ምድብ አሁንም መጨረሻው አልታወቀም።   ህዳር 29/2005 የተጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሴቶች ውድድር ሶስተኛ ሳምንት ቅዳሜና እሁድ ማለትም ታህሳስ 13 እና 14/2005 ቀጥሎ ተካሂዷል። በቅዳሜው ጨዋታ የማእከላዊ ዞን ምድብ አንድ ሁለት ጨዋታዎች ተከናውነዋል። በዚህም ደደቢት ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 0 በመርታት ምድቡን በዘጠኝ ነጥብ 1ኛ ሆኖ ያጠናቀቀበትን ውጤት ይዞ ወጥቷል። መብራት ሃይልን 3 ለ 1 የረታው ኢትዮጵያ መድህንም በ6 ነጥብ ሁለተኛ ሆኖ ሩበ ፍፃሜ መግባቱን አረጋግጧል። ኢትዮጵያ ቡናና መብራት ሃይል ከምድቡ ሳያልፉ ቀርተዋል። ቀሪ 4 ጨዋታዎች ደግሞ እሁድ ተከናውነዋል። በማዕከላዊ ዞን የምድብ ሁለት ጨዋታዎች በአዲስ አበባ ስታድየም ሲከናወኑ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢትዮጵያ ውሃ ስራዎች ላይ ከደርዘን በላይ ግቦችን አስቆጥሯል። ንግድ ባንክ 14 ለ 0 የረታበት ጨዋታ በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ግብ የተቆጠረበት ጨዋታ ሆኖ አልፏል። ከ14ቱ ግቦች ሽታዬ ሲሳይ በግሏ 7ቱን ግቦች ከመረብ ስታገናኝ፣ ረሂማ ዘርጋ 5ቱን በስሟ አስመዝግባለች። የሽታዬ ሲሳይ እህት የሆነችው ብዙነሽ ሲሳይ ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥራለች። በዚህም መሠረት ሶስቱንም ጨዋታዎች በአሸናፊነት የተወጣው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምድቡን በበላይነት አጠናቋል። በዚሁ ምድብ እኩል የማለፍ እድል ይዘው ወደ ሜዳ የገቡት መከላከያና የቅ/ጊዮርጊስ 1 ለ 1 ተለያይተዋል። ሁለቱም 4 ነጥቦችን በመያዝ መከላከያ የተሻለ የግብ ክፍያ ስላለው ንግድ ባንክን ተከትሎ ግማሽ

የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ ታሀሳስ 14/2005 የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ፡፡ የግንባሩ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው የፌዴራል መንግስት ተቋማትን የ2005 የዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍና ዋና ዋና የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በማስቀደም ነው የሁለት ቀናት ስብሰባውን የጀመረው፡፡ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከ2004 አፈጻጸም ግምገማ ከተለዩት ደካማና ጠንካራ የአፈጻጸም ውጤቶች በመነሳት የተካሄደውን የዕቅድ ዝግጅትና ፈፃሚ የማዘጋጀት ሂደት ፈትሿል፡፡ በዝግጅት ምዕራፍ ፈጻሚ የማዘጋጀት ሂደት ሦስቱንም የልማት ኃይሎች ማለትም የድርጅትን፣ የመንግስትንና ዋናው ፈጻሚና ተጠቃሚ የሆነውን የሕዝብ አቅም በዝርዝር ለይቶ ለመገንባት የተደረገው ጥረት ከወትሮው የተሻለ አፈጻጸም የታየበት እንደሆነ አረጋግጧል፡፡ በተለይም በእያንዳንዱ ዘርፍ ከተልዕኮው አንጻር ተጠቃሚ ወይም ተገልጋይ የሆነውን የሕዝብ ወገን በዝርዝር ለይቶ ቀጣይነት ያለውና በተጠያቂነት ላይ የተመሰረተ የተሳትፎና የግንኙነት ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረው ጥረት መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የመንግስትን አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ በእስካሁኑ የተሻለ ርቀት ከሄዱት ዘርፎች ልምድ በመነሳት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በአጽንኦት አሳሰቧል፡፡ በዝግጅት ሥራው ተመስርቶ በየዘርፉ የተከናወኑትን አባይት የልማት ሥራዎችን የፈተሸው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ፈጣኑ የኢኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ ጤንነቱን ጠብቆ በመቀጠል ላይ መሆኑን ገምግሟል፡፡ የከተማውን ነዋሪ በተለይም አነስተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በመፈታተን ላይ የነበረው የዋጋ ግሽበት ቀደም ሲል ከ39 በመቶ በላ

“ገዥውን ፓርቲ የሚጠቅሙ እየመሰላቸው በምርጫ ወቅት ችግር የሚፈጥሩ አስፈጻሚዎች አሉ”

Image
አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከአራት ወራት በኋላ ሚያዝያ 6 እና 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን ግልጽና ተዓማኒ ለማድረግ ደፋ ቀና ማለት ጀመርኩ ካለ ሰነባብቷል፡፡ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት የምርጫ ቁሳቁሶችን ከማሳተም፣ ከማዘጋጀትና ከማሠራጨት ጐን ለጐን ደግሞ፣ ቀደም ብሎ ማከናወን ቢገባውም በምርጫው ዙሪያ ውይይትና ሥልጠና በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ቦርዱ እያደረጋቸው ከሚገኙት የምርጫ ክንውኖች መካከል ታህሳስ 7 እና 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል ለጋዜጠኞች የሰጠው የሁለት ቀናት ሥልጠና ተጠቃሽ ነው፡፡ ሥልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን መምህር ዶክተር ገብረ መድኅን ስምዖንና በተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ ናቸው፡፡ አቶ አስመላሽ “የኢትዮጵያ የምርጫ ሕግና አፈጻጸሙ” በሚል ርዕስ ባዘጋጁት ጥናታዊ ጽሑፍ ዙሪያ የምርጫ ቦርድ አባላትንና ሌሎች የምርጫ ክንውኖችን በሚመለከት ከሥልጠናው ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አቶ አስመላሸ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ ታምሩ ጽጌ እንደሚከተለው አዘጋጅቶታል፡፡ ጥያቄ፡- የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አባላት ገለልተኛ ናቸው ብለው ያምናሉ? አቶ አስመላሽ ፡- የምርጫ ቦርድ አባላት ገለልተኛ ናቸው ወይስ አይደሉም ለማለት ዋናውና አንዱ መሠረታዊ ጉዳይ፣ የሚለዩበትን መሠረታዊ ነገር መፈተሽ ነው፡፡ የምርጫ ቦርድ አ

የሕወሓት አብዮት ሰለባዎች.. የአዋሳ ከንቲባ አቶ ሽብቁ እስር ተፈረደባቸው

የሕወሓት አብዮት ሰለባዎች.. የአዋሳ ከንቲባ እስር ተፈረደባቸው   ከሰሞኑ በደቡብ ክልል ጉራ ፈረዳ ወረዳ የአማራ ክልል ተወላጆች ተባረው መሬታቸው ለሌሎች የስርዓቱ ደጋፊዎችና አባላት በሃራጅ መሸጡን ዘ-ሐበሻ ስትዘግብ ቆይታ ነበር። ከአዲስ አበባ የመንግስት ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዜና ደግሞ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ሰዎች መሬት የሸጡ የክልሉ ባለስልጣናት በሙስና ወንጀል ተከሰው እንደተፈረደባቸው ያትታሉ። የሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥር ዓት አብዮት ለስልጣኑ ታማኝ ያልሆኑትን በሙስና ሰብብ ሲበላ መቆየቱን ያስታወሱት አስተያየት ሰጪዎች በታምራት ላይኔ ጀምሮ በስዬ አብርሃ ለጥቆ አሁን የጸረ ሙስና ሕጉ የቂም በቀል መወጣጫ ሆኗል ሲሉ ይተቻሉ። ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም መሬት ለግለሰቦችና ድርጅቶች ሰጥተዋል በሚል የሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩ የቀድሞ የሃዋሳ ከተማ ከንቲባና ሌሎች ስድስት ተከሳሾች በእስራትና በገንዘብ መቀጣታቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እያዳነቁ ዘግበዋል።  በማዳነቂያ ዜናቸው ላይ “ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤት የማይፈቀድን ቦታ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፥ የተጻፈውን ዕገዳ በመጣስ የተለያዩ ግለሰቦች እና ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ስምንት ሰዎች መሬትበመስጠታቸው ነው የተከሰሱት (የተሰመረበትን ይመልከቱ)ሲሉ ነው የመንግስት ሚድያዎች የዘገቡት። እነዚሁ ሚዲያዎች ዘገባቸውን ሲያጥናቅር “የደቡብ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩትን ፥ አቶ ሽብቁ ማጋኔን ጨምሮ 6 ተከሳሾች ላይ ከአንድ እስከ ስምንት ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ2 እስከ 20 ሺህ ብር እንዲቀጡ፤ ፍርድ ቤቱ የክልሉ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ይግባኝ በጠየቀባቸው ፥ አቶ ሽብቁ ማጋኔ፣ አቶ እንድርያስ ፉ

በሃዋሳ ከተማ ስልጣንን ተገን በማድረግ ወንጀል የፈጸሙ የስራ ሃላፊዎች በእስራትና ገንዘብ ተቀጡ

አዋሳ ታህሳስ 12/2005 የሀዋሳ ከተማ ከንቲባና ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን አለአግባብ በመጠቀም መሬት ለግለሰቦችና ድርጅቶች ሰጥተዋል በሚል የሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩ የከተማው ከንቲባና ሌሎች ስድስት ተከሳሾች በእስራትና ገንዘብ እንዲቀጡ ተወሰነ። የደቡብ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ባስቻለው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበረውን ሽብቁ ማጋኔን ጨምሮ 6 ተከሳሾች ላይ ከስምንት ዓመት እስከ አንድ ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ20ሺህ እስከ 2 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል። ፍርድ ቤቱ የክልሉ ጸረሙስና ኮሚሽን ይግባኝ በጠየቀባቸው ሽብቁ ማጋኔ፣ እንድርያስ ፉላሳ፣ ጸጋዬ አረጋ፣ ጉደታ ጉምቤ፣ አስራት ግቻሞና ከበደ ካያሞ ላይ የእስራትና ገንዘብ ቅጣቱን የወሰነው የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ በመሻር ነው። ግለሰቦቹ ለባለኮከብ ሆቴሎችና ከፍተኛ ኢንቨስትመንቶች ካልሆነ በቀር የመኖሪያ ቤት ቦታ መስጠት እንደማይቻል ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የተጻፈውን ዕገዳ በመጣስ ለግለሰቦች እንዲሁም ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ስምንት ሰዎች መሬት በመስጠታቸው ቅጣቱ ተጥሎባቸዋል ብሏል። በዚሁ መሰረት የሀዋሳ ከተማ የነበረው ሽብቁ ማጋኔ ላይ የአምስት አመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራትና የአምስት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጫ ተጥሎበታል። የሃዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማትና አስተዳደር የስራ ሂደት ባለቤት የነበረው እንድሪያስ ፉላሳና በማዘጋጃ ቤቱ የመሬት ልማትና አስተዳደር የስራ ሂደት ባለሙያ የነበረው ጉደታ ጉምቤ እያንዳንዳቸው በ5 ዓመት ከ6 ወር እስራትና በ15 ሺህ ብር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። የታቦር ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማትና አስተዳደር ስራ ሂደት አስተባባሪ በነበረው አስራት ግቻ

በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመስማራት ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጪ የሚመጡ ባሀብቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የከተማው አስተደደር አስታወቀ፡፡

Image
ባለፉት አራት አመታት በከተማው በባለሀብቶች በተከናወኑ የኢንቨስትመንት ስራዎች ከ23ሺህ በላይ ነዋሪዎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ በሌላም በኩል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ባለሃብቶች በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንዲገቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል፡፡ የሀዋሳ ከተማ በሃገር አቀፍ ደረጃ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ከተሞች በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ሲሆን ለዚህም እንደምክንያት የሚነሳው ለንግድ እንቅስቃሴ የምትመች መሆኑና የሃይቅዳር ከተማ መሆኗ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከተማዋን የቱሪስት መዳረሻ፣ የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በተያዘው አመት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ ገልፀዋል፡፡ በተለይ ይህን ስራ የበለጠ ማስኬድ እንዲቻል ከተማውን የማስተዋወቅ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው አመልክተዋል፡፡ 4ኛው የከተሞች ሳምንት ተካሂዶ  ሃዋሳ ሁለት ዋንጫ በማግኘት አሸንፋ ከተመለሰች በሁዋላ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጭ በርካታ ባለሃብቶች ጥያቄ እያቀረቡ እንዳለ አቶ ዮናስ ገልፀዋል፡፡ በዚህም የከተማ አስተዳደሩ የተሻሉ አሰራሮችን በመዘርጋት ባለሀብቶችን ለማስተናገድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ በከተማዋ ባለፋት አራት አመታት ውስጥ ኢንቨስት ባደረጉ ባለሃብቶች ከ 23 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውንና ኢንቨስትመንት ይበልጥ በከተማዋ ለማስፋፋት ዘመናዊ ድረ ገጽ በመክፈት የማስተዋወቅ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩል በተለያዩ ወቅቶች የኢንቨስትመንት ቦታ ወስደው ያላለሙ ባለሃብቶች እንዳሉ አረጋግጠናል ያሉት አቶ ዮናስ፣ 60 ባለሀብቶችን አሰተዳደሩ ወደ ልማት እንዲገቡ ማወያየቱንና ከስምምነት ላ

ለትምህርት ስርዓታችን ህልውና ከፖለቲካዊ ብልጠት ይልቅ ብልህነት ያሻል

  Written by  የተከበሩ አቶ ሙሼ ሰሙ ትምህርት ዜጎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ በመቅረጽ ለራሳቸው፣ ለማህበረሰባቸውና ለሃገራቸው ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ የሚያግዝ የእውቀት ማሸጋገርያ ስልት ነው፡፡ የትምህርት መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ መጣል ከጀመረ ከመቶ ዓመታት በላይ የተቆጠረ ሲሆን ከሁለተኛው አለም ጦርነት በፊት ትምህርት የሚሰጠው በመንግስትና በሃይማኖት ተቋማት ዙርያ ለአስተዳደራዊ ክህሎት፣ ለቀኖናና ለሃይማኖት እውቀት ሲባል እንደነበረ እ.ኤ.አ 2004 ላይ ዮኔስኮ የትምህርት ስርዓትን አስመልክቶ ባዘጋጀው ኮንፍረንስ ላይ የወጡ ዘገባዎች ይገልጻሉ፡፡ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ የአፄ ሃይለ ስላሴ ስርዓት ዘመናዊ ትምህርትን በተደራጀ መልኩ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲሰጡ ሁኔታዎችን ያመቻቸ ቢሆንም የትምህርት ቤቶች እድገት ከማህበረሰቡም ሆነ ከሃይማኖት ተቋማት በገጠመው ተጽእኖ ምክንያት የመስፋፋቱ እድል አዝጋሚ ሆኖ ቆይቷል፡፡ የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል የተደረጉ ተከታታይ ጥረቶችም በወቅቱ ከተከሰተው ኢኮኖሚያዊ ቀውስና ድርቅ ጋር ተዳብለው ለአፄው ስርዓት ውድቀት ምክንያት ሊሆን ችሏል፡፡ ለደርግ በወቅቱ የነበረው አጣዳፊ ጉዳይ አብዮቱ በመሆኑ በመማርና ማስተማር ላይ የነበሩትን መምህራንና ተማሪዎች በነቂስ አሰልፎ አብዮቱን ለማስተዋወቅ በሚል ሰበብ ወደ እድገት በሕብረት የዕውቅትና የስራ ዘመቻ አዘመተ፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ እራሱን በጥቂቱም ቢሆን ማጎልበት የጀመረው የትምህርት ስርዓት ከባድ ፈተና ውስጥ ወደቀ፡፡ ከየመንግስት መስርያ ቤቱና ተቋማቱ ሁሉም ዓይነት ባለሙያዎች በወረንጦ እየተለቀሙ የማስተማር ሂደቱን በግድ እንዲቀላቀሉ ተደረገ፡፡ እዚህ ላይ የመምህርነትን ሙያ በፍቅር ሳይሆን በተጽእኖ እንዲቀበሉ የተገደዱ ግለሰቦች ምን ዓይነት ትውልድ

Ethiopia Combating Stunting in Children in Aleta-Wondo Woreda town of the Southern Regional State of Ethiopia

Image
BY Mekonnen Teshome Adugna Mitiku had never realized the advantage of giving colostrum to her children within an hour of their birth and also did not exclusively feed her breast in the six months after their birth, contrary to doctors’ advice to help them physically and mentally develope. Adugna (Right) and her daughter Meron embracing her ten-month old son Rather Adugna, a resident in 04 Dela Kebele of the Aleta-Wondo Woreda town of the Southern Regional State of Ethiopia, spilled out the colostrum before feeding breast her daughters as she thought it was something unclean and unpleasant for them to take against the teaching of health professionals. She also gave her babies Hamessa, juice of a “medicinal” plant that usually affects newborn babies’ kidney, with in few hours of their birth thinking that it would make the newly born babies strong and healthy according to the tradition of her society. She also didn’t start complementary food when they get six months old

የጋዜጠኞች መገደል

Image
ሃያ-ስምንት የኤርትራ ጋዜጠኞች በዳርዊሽ ቋንቋ «የማያዉቁትን ፈንጂ ረግጠዉ» ከማይታወቅ ሥፍራ ከተከረቸሙ ዓመታት አልፏቸዋል።ዳ ብዙ ኢትዮጵያዉያን ጋዜጠኞች እስር ቤቶችን ተመላልሰዉባቸዋል። ዉብሸት ታዬ፥ ርዕዮት ዓለሙ፥ እስክንድር ነጋ እና ሌሎችም ዛሬም በየወሕኒ ቤቱ ይማቅቋሉ። 19 12 12 የተገባደደዉ የጎርጎሮሳዉያኑ ዓመት 2012 ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ጋዜጠኞች የተገደሉበት፥ በርካቶች የታሠሩ ወይም የተንገላቱበት ዓመት እንደሆነ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች አስታወቁ።ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች የተሰኘዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅትና ሌሎች ተቋማት እንዳስታወቁት የግብፅ ሕዝባዊ አብዮት፥ የሶሪያዉ ጦርነት፥ የሶማሊያ ግጭት ለበርካታ ጋዜጠኞች ሞት ምክንያት ሆኗል።እንደ ጎሮጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ከ1995 ወዲሕ በአንድ ዓመት ዉስጥ በርካታ ጋዜጠኞች ሲገደሉ ዘንድሮዉ ከፍተኛዉ ነዉ።ነጋሽ መሐመድ አጭር ዘገባ አለዉ። «ሶሪያ ዉስጥ ጋዜጠኛ መሆን ፈንጂ በፈሰሰበት ምድር እንደመራመድ ነዉ።ብዙ የማይነኩ ነገሮች አሉ።አንዳዶቹ ለምሳሌ ፖለቲካዊ፥የሰብአዊ መብቶች ወይም የሥርዓቱ ባሕሪያት የመሳሰሉት ርዕሶች በግልፅ ይታወቃሉ።ሌሎች ደግሞ ቀይ መስመራቸዉ የማይታወቅ ግን አይነኬ ብዙ ጉዳዮች አሉ።እና ፈንጂዉን መቼ እንደምትረገጠዉ፥መቼ እንደሚፈነዳም የሚያዉቅ የለም» ብሎ ነበር። ሶሪያዊዉ ጋዜጠኛ ማዘን ዳርዊሽ፥-ሐቻምና መጋቢት። ዳርዊሽ ፈንጂዉን እንዴት እንደረገጠዉ በርግጥ የሚያዉቅ የለም።ብቻ ፈነዳ። ግን አልገደለዉም። ካልታወቀ ስፍራ-አሳሰረዉ እንጂ።ዳርዊሽ የዘንድሮዉን የድንበር የለሽ ዘጋቢዎችን ሽልማትን አግኝቷል። ሕይወትን ለሙያ ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች እንደሚለዉ ሃያ-ስምንት የኤርትራ ጋዜጠኞች በዳርዊሽ ቋንቋ «የማያዉቁትን ፈንጂ ረግጠዉ» ከማይታወቅ ሥፍ

የጊዳቦ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት 47 ነጥብ 80 በመቶ መጠናቀቁ ተገለፀ

Image
አዲስ አበባ፤ ህዳር 10/2005(ዋኢማ) -  በኦሮሚያና በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በመገንባት ላይ ያለው የጊዳቦ የመስኖ ልማት ግድብ ፕሮጀክት 47 ነጥብ 80 በመቶ መጠናቀቁን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ በዘንድሮው የበጀት ዓመትም የጊዳቦን የመስኖ ልማት ግድብ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ ታቅዷል። የጊዳቦ የመስኖ ግድብ ፕሮጀክት በ303 ሚሊየን 386 ሺ ብር በ2002 ዓ.ም ጥር ወር ላይ ግንባታው የተጀመረ መሆኑን ገልፀው፤ በዘንድሮው የበጀት ዓመት መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ብዙነህ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ለማጠናቀቅም በዘንድሮው የበጀት አመት 95 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ የቁፋሮ፣ የግድብ አፈር ሙሌት፣ ቁፋሮ፣ የኮንክሪት ስራና የውሃ ማውጫ ግንባታ ቁፋሮና ኮንክሪት ሙሌት ስራዎችን ለማጠናቀቅ ታቅዷል ብለዋል። ግድቡ 20 ነጥብ 80 ሜትር ከፍታ የሚኖረው ሲሆን ርዝመቱም 269 ሜትር እንደሚኖረው ጠቁመው፤ ግድቡ ሲጠናቀቅም  117 ነጥብ 82 ሚሊየን ሜትር ኩብ ውሃ የማጠራቀም አቅም እንደሚኖረው ተናግረዋል። ይህም 7 ሺ 374 ሄክታር መሬትን በመስኖ ሊያለማ የሚችል ሲሆን፤ በዚህም 79 ሺ 820 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ሊያደርግ እንደሚችል አቶ ብዙነህ ገልፀዋል። የግንባታ ማሽነሪዎች አቅርቦት አናሳ በመሆኑና የአካባቢው የክረምት ወቅት መርዘምን ተከትሎ በተፈለገው ፍጥነት ለመስራት አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት በሚፈለገው መጠን ፕሮጀክቱ እየሄደ አለመሆኑን ጠቁመው፤  ችግሩን በመፍታት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ውስጥ ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆ

መገናኛ ብዙኃን ምርጫውን በትክክል በመዘገብ ሚናቸውን እንዲወጡ ተጠየቀ

Image
ፕሮፌሰር መርጋ በቃና፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በ 2005  ዓ . ም የሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ አስተዳደር ምርጫን ትክክለኛ ገጽታ በመዘገብ አገራዊ ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው ተገለጸ። በምርጫ ሕጎች አሠራሮችና በምርጫ አዘጋገብ ላይ ለመገናኛ ባለሙያዎች ለሁለት ቀናት የተዘጋጀ ሥልጠና ትናንት ሲጀመር የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንደተናገሩት፤ ባለሙያዎቹ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ለዜጎች በማድረስ ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ የበኩላቸውን ሚና ሊጫወቱ ይገባል። እንደ ፕሮፌሰር መርጋ ገለፃ፤ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት በምርጫው ወቅት ለሕዝቡ ከወገንተኝነት የፀዳ መረጃ ይጠበቅባቸዋል። ዜጎች በሕገ መንግሥቱ የተጎናፀፉትን የመምረጥና የመመረጥ መብት እንዲጠቀሙ ማነሳሳት አለባቸው። በመሆኑም ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ከምርጫ ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጋቸው ይህን ከግቡ ለማድረስ እንደሚያስችል ፕሮፌሰሩ አመልክተዋል። የሥልጠናው ዓላማ ጋዜጠኛው በምርጫው ላይ ያለው የአዘጋገብ ክህሎትን የሚያስጨበጥ እንደሆነ አመልክተው፤ እንዲሁም ልምዳቸውን የሚለዋወጡበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ፓርቲዎችም ሆነ የግል ተወዳዳሪዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ በሚያደርጉበት ወቅት መተባበርና መቻቻል እንዲኖራቸው፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴውን ሳያውኩ በሥነ ምግባር ሕጉ መሠረት እንዲያካሂዱ የማድረግ አገራዊ ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። የሥልጠናው ተሣታፊዎች የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን ጨምሮ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን የየክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ባለሙያዎች እንዲሁም የጋዜጠኞች ማኅበራት ተወ

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከፍተኛ የመንግሥት ፕሮጀክት ግዥዎችን እመረምራለሁ አለ

Image
-    ስዊስ ባንክ በታምራት ላይኔ ስም የተቀመጠ ስምንት ሚሊዮን ዶላር መለሰ በውድነህ ዘነበ በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ግዙፍ የመንግሥት ፕሮጀክቶች ከሚያካሂዷቸው ግዥዎች ጋር በተያያዘ የሙስና ሥጋት በመፈጠሩ፣ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ እጀምራለሁ አለ፡፡ ኮሚሽኑ ምርመራ ከሚያካሂድባቸው ፕሮጀክቶች መካከል በስኳር ኮርፖሬሽን አማካይነት የሚካሄዱ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የሚካሄዱ ትላልቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦችና ጣቢያዎች ግንባታና በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የሚካሄዱ ትላልቅ የኢንጂነሪንግ ፕሮጀክቶች ይጠቀሳሉ፡፡ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ በትላልቅ የመንግሥት ፕሮጀክቶች ላይ እንዲያተኩር መመርያ ተሰጥቶታል፡፡ “ቀደም ሲል ከምናካሂደው በተለየ ሁኔታ በግዙፍ ፕሮጀክቶች ግዥ ላይ እናተኩራለን፤” ሲሉ አቶ ዓሊ ገልጸዋል፡፡ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ በመቶ ቢሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ በርካታ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ላይ መሰማራቱ ይታወቃል፡፡ በእነዚህ ግዙፍ መንግሥታዊ ፕሮጀክቶች ላይ ምርመራ ለማድረግ እየተዘጋጀ ያለው የፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ ለምርመራው ያለውን የሰው ኃይል እንደሚያሰማራ ተገልጿል፡፡ ጥቃቅን የሙስና ወንጀሎችን እንጂ ታላላቅ ሙስናዎች አይደፍርም በሚል የሚታማው ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ ዘግይቶም ቢሆን በእነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ ምርመራ ለመጀመር መዘጋጀቱ መልካም ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን የሽግግሩ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ከነበሩት አቶ ታምራት ላይኔና የመከላከያ ሚኒስትር ከነበሩት አቶ ስዬ አብርሃ ወዲህ፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በሙስና ባለመጠየ