Posts

Showing posts from November, 2012

በሀዋሳ ከተማ ከ210 ሚልዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የልማት ስራዎች እየተካሄዱ ናቸዉ -በከተሞች ሳምንት ላይ ለተሳተፉ የምስክር ወረቀት ተሰጠ

Image
አዋሳ ህዳር 21/2005 በሀዋሳ ከተማ ከ210 ሚልዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የከተማው አስተዳደር ገለጸ፡፡ በአራተኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ሀዋሳ ከተማ ላስመዘገበችው አመርቂ ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት፣ ድርጅቶች፣ ማህበራትና ግለሰቦች ትናንት ምሽት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡ የከተማው ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ በዚሁ የምስጋና ፕሮግራም ላይ እንደተናገሩት ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ፣ የኢንቨስትመንት ተመራጭ እንዲሁም የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በርካታ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸዉ ። ሀዋሳ ውብ፣ ጽዱና አረንጓዴ፣ በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ ገጽታዋ የጎላ እንዲሆን የቱሪስት ፍሰቱ እንዲጨምር፣ የንግድና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ። በከተማ አስተዳደር፣ በማዘጋጃ ቤት የውስጥ ገቢ፣ በመንግስት መደበኛ በጀትና ከአጋር ድርጅቶች በተመደበው 210 ሚልዮን ብር ወጪ እየተካሄዱ ያሉት 10 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ፣ ከ45 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ የጠጠርና የኮብል ስቶን ንጣፍ ናቸዉ ። በተጨማሪ የባህል ማዕከል፣ ዘመናዊ የመንገድ ላይ መብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታዎች፣ እንዲሁም ዘመናዊ ቄራ ግንባታ በዋናነት እንደሚገኙበት አቶ ዮናስ ተናግረዋል፡፡ ከመሰረተ ልማት ግንባታዎች ውስጥ እስከ አሁን አብዛኛዎቹ ከ50 በመቶ በላይ መከናወናቸዉንና በጀት ዓመቱ ከፍፃሜ ለማድረስ ጥረት ከወዲሁ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ታገሰ ጫፎ ለተቋማቱ፣ ድርጅቶችና ማህበራት ሰርተፍኬት ከሰጡ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት በአመራሩና ከተማ ነዋሪዎች የጋራ ጥረት የተመዘገበ ውጤት በ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአምስት ሚኒስትሮች ሹመትን አጸደቀ

Image
አዲስ አበባ ህዳር 20/2005 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስት የፌዴራል አስፈጻሚ አካላት የሥራ ኃላፊዎች ሹመትን አጸደቀ። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው የ3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባ የሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የንግድ ሚኒስትርና የጤና ጥበቃ ሚኒስትሮችን ሹመት አጽድቋል። በዘህም መሰረት አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር፣ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን መገናኛና ሚኒስትር በመሆን ተሹመዋል። ይህም ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች እንዲኖሯት ያስቻለ ሹመት ሆኗል፡፡ እንዲሁም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩት ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የንግድ ተጠባባቂ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ከበደ ጫኔ የንግድ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል። ተሿሚዎቹ በትምህርት ዝግጅታቸው፣ በፖለቲካ አመራር ብቃታቸውና ባላቸው የስራ ልምድ ለኃላፊነቱ የተመረጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት አሁን የተካሄደው ሹመት የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ለማጠናከር፣ የተሻለ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብና የመተካካት ሥርዓቱን ለማጎልበት ነው። ሹመቱ በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በአብላጫ ድምጽ የጸደቀ ሲሆን ተሿሚዎቹም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በአቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ በተጨማሪ ምክር በኢትዮጵያ መንግሥትና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካካል 4ኛውን የመንገድ ዘር

“ሕዝቡ ከማጉረምረም አልፎ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነ አይመስልም” ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፤ ሲዳማም ውስጥ ያለው እውኔታ ይሄው ነው

Image
በኣጠቃለይ በኢትዮጵያ ደረጃ በኣገሪቱ ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚሉት ከሆነ ህዝቡ በመልካም ኣስተዳደር ይዞታ ላይ ያለውን ቅሬታ ኣውጥቶ  ለመናገር ወነ ያጣ ሲሆን ተመሳሳይ ሁኔታ በሲዳማ ውስጥም በመከሰት ላይ ነው፤ ምናልባት የሲኣን በኣዲስ ኣመራር መዋቀር ህዝቡን ከላነቃቃው በስተቀር ማለት ነው። በኣጠቃላይ ኣገሪቱን በተመለከተ ዝርዝሩን ከታች ያንቡ።  ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር -    ኢሕአዴግ ለሕዝብ ደንታ የለውም አሉ -    ብልሹ የምርጫ ሥርዓት መስፈኑን ወቀሱ በጋዜጣው ሪፖርተር ባለፈው እሑድ ኅዳር 16 ቀን 2005 ዓ.ም. አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባደረገው ውይይት ላይ የመነሻ ሐሳብ ያቀረቡት የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሶተኛና በማጉረምረም ደረጃ ላይ የሚገኝ እንጂ፣ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነበት ደረጃ ላይ የደረሰ አይመስልም አሉ፡፡ የአገሪቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ በዳሰሱበት ክፍል ላይ በሰጡት ማብራሪያ ሕዝቡ በርካታ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንዳሉበት ገልጸው፣ ይህንን ሰቆቃውንና ብሶቱን ያማርራል እንጂ በይፋና በአደባባይ አይገልጽም ብለዋል፡፡ “ብሶቱ በማጉረምረም ደረጃ የሚገለጽ ነው እንጂ ወደ ኅብረተሰባዊ ንዴት አልተለወጠም ብለው፣” የተናጠል ንዴቶች አልፎ አልፎ ቢገለጹም ሰፊና የአጠቃላይ ኅብረተሰቡ አለመሆናቸውን አመልክተዋል፡፡ “እነዚህ የተናጠል ትናንሽ ንዴቶች ወደተደራጀና ሕዝባዊ የእምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች አልተለወጡም፡፡ በሌሎች አገሮች በዳቦ ወይም በነዳጅ ዋጋ ላይ ትንሽ ጭማሪ ከታየ የኅብረተሰቡ ንዴት ይገነፍላል፡፡ በእኛ ሕዝብ ዘንድ ግን ይህ አይታይም፡፡ ምልክቶች ከታዩ ጥቂ

80 ኪሎ ሜትር መንገድ በዳራ ወረዳ በመገንባት ላይ መሆኑ ተሰማ

Ethiopia: Road Building Accord Addis Ababa — A contract agreement providing for building the roads linking the country's road network with three new sugar factories at a cost of over 3.9 billion birr was signed here yesterday. Similarly, 80-kms road is being constructed in Dara Woreda , Sidama Zone of Southern Nations, Nationalities and Peoples State at a cost of over 40 million birr allocated by the government, the Woreda's Road Transport Office said. Ethiopian Roads Authority Director-General Zayid Wolde-Gebriel and General Manager of China Communications Construction Company (CCCC) Group Zhou Yongsheng and CGC Overseas Acting General Manager Gao Lei. The roads linking Enjibara-Chagni- Pawe, Pawe-Fendiqa Ayma and Kesem Sugar Factory will be upgraded to asphalt concrete level. CCCC will construct the 100-kms Enjibara-Chagni- Pawe road with over 2.2 billion birr. CGC Overseas will also construct the 75-kms Pawe-Fendiqa Ayma road and the 22-kms road leading to Kes

የሲዳማ ቡና መዓዛና ጣዕም ያለው ቢራ መመረት መጀመሩ ከወደ ኣሜሪካ ተሰማ

Image
Get ready to wake up and face the coming winter days with a pint of Aces and  Ates  stout. Raleigh’s Big Boss Brewery has rolled out their winter stout, Aces and  Ates , and it sure is tasty. Created by one of Big Boss’ founders, Brad Wynn, Aces is a beer that will wrap its big hairy arms around you during the long and lonely winter nights. Traditionally stout beers referred to the strongest porter beers a brewery had to offer, often boasting seven percent to eight percent alcohol by volume. Big Boss’ winter seasonal offering comes in around nine percent  abv . “[Aces and  Ates ] is an American stout in the sense that it’s not using classic Irish yeast,” Brooks Hamaker , operations manager at Big Boss Brewery, said. “It is very rich; it lends itself to coffee very well. The body of beer is relatively heavy, and coffee is, or can be relatively heavy. And the two just blend really well and people just like it. It’s a great Saturday morning beer, before a football game, for exam

አዲሱ ጠ/ሚንስትርና የአዲስ ካቢኔ ጉዳይ

Image
አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሀገሪቷን ለመምራት ቃለ-መሃላ የገቡት ባለፈው መስከረም ወር እንደነበረ የሚታወስ ነው። አቶ ኃይለ-ማርያም፤ ወደ ሥልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ ካቢኔያቸውን ለኢትዮጵያ ፓርላማ ያቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ፣ በይፋ ሲከናወን አልታየም። በተለይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ሥልጣን የያዘው ሰው እስካሁን ግልጽ አልተደረገም። የካቢኔው ይፋ አለመሆንና በተለይም የውጭ ጉዳይ እስካሁን አለመሾሙ ምክንያቱ ምን ይሆን? በዚሁ ጉዳይ ላይ ገመቹ በቀለ ፣ ኒውዮርክ ከሚኖረው ወጣት የፖሊቲካ ተንታኝ ፣ጀዋር መሐመድ ጋር ቃለምልልስ አድርጓል። አዲሱ ጠ/ሚንስትርና የአዲስ ካቢኔ ጉዳይ

ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ምርትና ምርታማነት በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የግብርና ቴክኖሎጂ እያስተዋወቀ ነው

Image
አዋሳ ህዳር 18/2005 የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከ11 የሚበልጡ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማስተዋወቅ ላይ እንደሚገኝ የሀዋሳ ዩነቪርስቲ ገለጸ፡፡  በዩኒቨርስቲው በሲዳማና ገዴኦ ዞኖች በሙከራ ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ቴክኖሎጅዎችን የማላመድ፣ የማስተዋወቅና የማስፋፋት ስራዎች ሰሞኑን ተጎብኝቷል፡፡ የዩኒቨርስቲ አካዳሚና ምርምር ምክትል ፕሬዜዳንት ዶክተር ፍቅሬ ደሳለኝ በጉብኝት ወቅት እንደገለጹት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መጨረሻ የግብርና ምርት በእጥፍ ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ዝርያዎችን ለማላመድና ማስፋፋት ስራ ዩኒቨርስቲው ትኩረት ተሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርስቲው በሀገሪቱ የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ የሚያግዙና በምርምር ጣቢያ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ 11 ዝርያዎችን በክልሉ አራት ወረዳዎች የማባዛትና የማላመድ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በልጆች ላይ የሚከሰተውን የቫይታሚን ኤ ንጥረ ምግብ እጥረት የሚከላከሉ ሰብሎች፣ የቤተሰብ ገቢና የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል የሚያግዙ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ፣ የአንስሳት መኖ፣ ሀገር በቀል የበግና ፍየል ዝርያዎችን የማዳቀልና ማባዛት እንዲሁም መኖን በዩሪያ ማከምና ድርቆሽ ሳይበላሽ የማቆየት ዘዴዎች ይገኙበታል ብለዋል፡፡ በሄክታር እስከ 50 ኩንታል ምርት ሊሰጡ የሚችሉ የቢራና የምግብ ገብስ፣ ባቄላና ሌሎች የሰብል ዝርያዎች የሚገኙ ሲሆን በብተናና በመስመር የመዝራት ልዩነትና ከዚሁም ሊገኝ የሚችሉ ጠቀሜታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ በንጥረ ምግብ ይዘት የበለፀጉ የደጋና የወይና ደጋ የጥራጥሬ ሰብሎችን በማምረት የቤተሰብ የንጥረ ምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል፣ ናይትሮጂን ወደ ራሳቸው በማዋ

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ኢትዮጵያ ቡና እና ሀዋሳ ከነማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

Image
በ7ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ህዳር 16/2005  በተለያዩ ከተሞች አምስት ጨዋታዎች ተካሂደዋል። አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ በ8 ሰዓት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሙገር ሲሚንቶ ተገናኝተው 2 አቻ በሆነ ውጤት ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል። ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ታዬ አስማረ እና ሳምሶን ሙሉጌታ ሲያስቆጥሩ ለሙገር ሲምንቶ እስክንድር አብዱአሚድ እና አዲሱ ዋናሮ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። 10 ሰዓት ላይ የተደረገው ኢትዮጵያ ቡና እና ኢትዮጵያ መድህን ያደረጉት ጨዋታ በኢትዮጵያ ቡና 4 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል። ለኢትዮጵያ ቡና ታፈሰ ተስፋዬ ፣ሰለሞን ገብረመድህን ፣ቶክ ጀምስ እና ፋሲል አስፋው ጎሎቹን አስቆጥረዋል።አራቱም ጎሎች በመጀመሪያው አጋማሽ ነው የተቆጠሩት። ኢትዮጵያ መድህን ሁለተኛው ግማሽ ላይ በመሐመድ ናስር የማስተዛዘኛውን ጎል አስቆጥሯል። በመብራት ኃይል እና በመከላከያ መካከል የተደረገው ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ጨዋታው በተጀመረው በአራተኛው ደቂቃ መብራት ኃይል በበረከት ይሳቅ የመጀመሪያውን ጎል በማስቆጠር መሪ መሆን ቢችልም መከላከያ ሁለት ጎሎችን በዮሐንስ ኃይሉ አስቆጥሮ እረፍት ወጥቷል። የመብራት ኃይሉ በረከት ጎል ሊሆኑ የሚችሉ አጋጣሚዎች ሳይጠቀምበት ቀርቷል። ሁለተኛው አጋማሽ ላይ መብራት ኃይል ያገኛትን የፍፁም ቅጣት ምት አዲስ ነጋሽ አስቆጥሮ አቻ ወጥቷል። ሀዋሳ ላይ ሀዋሳ ከነማ የኢትዮጵያ ውሃ ሰራዎችን አስተናግዶ 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲረታ። ሀረር ቢራ ከሲዳማ ቡና 1 አቻ በሆነ ውጤት ነጥብ ተጋርተዋል። ውጤቱን ተከትሎ ሀዋሳ ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ በ13 ነጥብ በሁለተኛነት የሊጉን ደረጃ ይዟል። መብራት ኃይል ፣ኢትዮጵያ ቡና ፣ ሀረር ቢራ

በጃፓን የኢፌዴሪ የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ተከፈተ

Image
አዲስ አበባ፡- በጃፓን ናጎያ ከተማ የኢፌዴሪ የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤት መከፈቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ለጋዜጣው በላከው መግለጫ፤ ጽሕፈት ቤቱ በተከተፈበት ወቅት በጃፓን የኢፌዴሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ «ኢትዮጵያ ነፃነቷን አስጠብቃ የቆየችና ለጥቁር ሕዝቦች ነፃነትና ፓን አፍሪካኒዝም የጐላ ሚና የተጫወተች ሀገር ናት» ማለታቸውን አስታውቋል። በአሁኑ ወቅትም ሠላምና መረጋጋት የሰፈነባት ከመሆኗም ባሻገር ልማቷን በማፋጠን ድህነትን ድል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰች መሆኑ ተጠቁሟል። እንደ አምባሳደር ማርቆስ ገለጻ፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረ ነው። ጃፓን በጠንካራ አጋርነቷ በተለይም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነትን ከፍ በማድረግና በጐ ፈቃደኞችን በመላክ የቴክኒክና ዕውቀት ሽግግር እንዲስፋፋ አስተዋፅኦ እያበረከተች ነው። በጃፓን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ቪንቺ አሳዙማ በበኩላቸው፤ ጃፓንና ኢትዮጵያ ረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አመለክተው፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን እያደረገች ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቀጣይ በምታዘጋጀው ለአፍሪካ ልማት የቶክዮ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይም ጠንካራ አስተዋፅኦ እንደሚኖራት ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል። የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤቱ መከፈት ሁለቱ አገራት ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የራሱ አስተዋፅኦ እንዳለው አመልክተዋል። በዕለቱ በጃፓን የኢትዮጵያ መንግሥት የክብር ቆንስላ ሆነው እንዲሠሩ የተመረጡት ሚስተር ላዲማቺ ማትሲሞት የሹመት ደብዳቤ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማን ከአምባሳደር ማርቆስ ተክሌ እጅ ተረክበዋል።

ብሄራዊ የስነ- ህዝብ ምክር ቤት ሊቋቋም ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በያዝነው ዓመት የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር 84 ነጥብ 3 ሚሊዮን ገደማ መድረሱን ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ያደረገው ሳይንሳዊ ግምት ያመለክታል። የሃገሪቱ ፖሊሲ የህዝብ ቁጥርን መቀነስ ላይ ከማተኮር ይልቅ ፥ ያለውን የህዝብ ቁጥር ከሃገሪቱ የልማት አቅምና የኢኮኖሚ ክፍፍል ጋር ማጣጣም ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው። ኢትዮጵያም የህዝብ ቁጥሩን ዕድገት ከኢኮኖሚ ዕድገቷ ጋር ለማመጣጠን እንዲያስችላት ፥ ከዛሬ 18 ዓመት በፊት የስነ-ህዝብ ፖሊሲ ቀርጻ ወደ ትግበራ ብትገባም ፥ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገም። ይህንኑ የስነ-ህዝብ ጉዳይ የሚያስተባብረውን የብሄራዊ ስነ-ህዝብ ምክር ቤት ለማማቋም ፥ ባለፈው አመት ረቂቅ ደንብ በማዘጋጀት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን ፤ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ተጠባባቂ የስነ-ህዝብ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መኮንን ናና ተናግረዋል። እሳቸው እንዳሉት የሚቋቋመው ምክር ቤት ይበልጥ ውጤታማ ይሆን ዘንድ ፥ እንደገና ሰፋ ያለ ጥናት ተደርጎበት ፤ በዚህ አመት መጨረሻ ወይም በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ላይ ፥ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይቀርባል። ረቂቁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ አስኪጸድቅ ድረስም ፥ የማስተባበሩን ሒደት ለማከናወን ሃገር አቀፍ ግብረ ሃይል በያዝነው ወር ውስጥ በማቋቋም ፥ ምክር ቤቱ እስኪመሰረት ግብረ ሃይሉ የማስተባበሩን ስራ እያከናወነ ይቆያል ብለዋል አቶ መኮንን። ሃገሪቱ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ባለሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት ብታስመዘግብም ፥ ካላት የህዝብ ብዛት ጋር መመጣጠን ባለመቻሉ አጠቃላይ የምርት መጠኗ 412 አሜሪካን ዶላር ላይ እንዲወሰን አስገድዷታል። የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያመለክተው ደግሞ ፥ በሃገሪ

የሲኣን ምስረታ በኣል እና ኣዲስ ኣመራር

ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ  SLM (Sidama liberation movement) is transformed! Today is the day of transformation for SLM and/or Sidama As many sons, daughters and friends of Sidama have been writing and speaking in several medias, occasions, and moments the oppression, terrorism, and agony caused by the tyrant rulers of the past governments including the present one is immeasurable. Since the hands of occupiers had touched the land of Sidama, the people has been fighting and saying no to forceful occupation. Even after the consolidation of the power of the tyrants the people of Sidama hasn’t kept silent. Injustices and lack of good governance and basic human rights violations has been the concern of the entire Sidama. Today I am writing not to mention the injustices and immoral acts of the government.  I would like to take this opportunity to write little about today’s organized resistance response of our people. Of course our people had resisted the occupiers in an organized way incl

ተቃዋሚዎች ከኢህአዴግ ጋር ድርድር እንፈልጋለን አሉ

Image
በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ከመወያየታችን በፊት በምርጫው ዲሞክራሲያዊነትና ነፃ መሆን ላይ ልንወያይ ይገባል በሚል ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ጥያቄ ያቀረቡ 34 ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባሉን ተቃወሙ፡፡ በምርጫ ቦርዱ ላይ እምነት ስለሌለን ከኢህአዴግ ጋር ያለቅድመ ሁኔታ ድርድር እንፈልጋለን ብለዋል - ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ፡፡የኢህአዴግ ጽ/ቤት ቢሮ ኃላፊና በጠ/ሚኒስትሩ የህዝብ አደረጃጀት አማካሪ አቶ ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፤ የምርጫ ስነምግባር ደንቡን ካልፈረሙ ፓርቲዎች ጋር አንደራደርም ብለዋል፡፡  ፓርቲዎች የምርጫ ምልክታቸውን እስከፊታችን ሰኞ እንዲወስዱ ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፤ ለቦርዱ ደብዳቤ በማስገባት ምላሽ እየጠበቁ ባሉበት ሰዓት የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባላቸው አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ተቃዋሚዎች ላቀረቡት ጥያቄ ምርጫ ቦርድ “ምላሽ የሚሰጠው ተገቢ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ ነው” ሲል ለአዲስ አድማስ መግለፁ ይታወሳል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በቦርዱ ላይ እምነት እንደሌላቸው በመግለፅ፡- ከኢህአዴግ ጋር ውይይት እንደሚፈልጉና ከዛ በፊት የምርጫ ምልክት እንደማይወስዱ አስታውቀዋል፡፡ የመድረክ የስራ አስፈፃሚ አባልና የ34ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ ሲያስረዱ፤ “ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎች ችግር የነበረባቸው በመሆናቸው ከጊዜ ሰሌዳው በፊት በምርጫው ፍትሃዊነትና ዲሞክራሲያዊነት ላይ ውይይት እንዲደረግ ፒትሽን ተፈራርመን ለቦርዱ አስገብተን፣ ለሱ ምላሽ ሳይሰጥ ምልክት ውሰዱ መባሉ ተገቢ አይደለም” ብለዋል የምርጫ ቦርዱ ተአማኒነትና ተቀባይነት ጥያቄ ውስጥ ነው ያሉት አቶ አስራት ጣሴ፤ ከኢህአዴግ

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል በዛሬው እለት በሃዋሳ ከተማ በዳግም ጂሚናዥዬም በተካሄደው የምስረታ  ሰነስርኣት ላይ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ  35 ኣመት የምስረታ በኣል በተለያዩ  ዝግጅቶች ኣክብሯል። በርካታ የድርጅቱ ደጋፊዎች በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ስነስርኣት ላይ ለሲዳማ ህዝብ ነጻነት ለተሰው ሰማዕታት የህልና ጸሎት የተደረገ  ሲሆን ድርጅቱን በቀጣይነት የምመሩ ኣመራሮች ተመርጠዋል። በኣጠቃላይ 15 ኣባላት ያሉት በኣብዛኛው ወጣቶችን የሆነና የዩኒቨርሲቲ ተማርዎችን ያቀፈ የድርጅት ኣመራር የተመረጠ ሲሆን ኣንጋፋ የሲዳማ ታጋዮችን በኣመራርነት ተካተዋል። በኣመራርነት ከተመረጡት መካከል ካላ ዋቃዮ፤ ዶክተር ኣለማዬሁ፤ እና ካላ ካሳ ኣዲሶ  ይገኙበታል። ክቡራን ኣንባቢያን  ዝርዝር ዜናውን እንደደረሰን እናቀርባለን

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ሀይለኢየሱስ እንደገለፁት መንግስት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በነደፈው ስትራቴጂ መሠረት በተያዘው በጀት ዓመት 1ዐ ሚሊዮን ብር ብድር ለማሰራጨት እና 18 ሚሊዮን ብር ከቁጠባ ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ ነው፡፡ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከንግድና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዩንቨርስቲዎችና ኮሌጆ  ለተመረቁ  ተማሪዎችን ከ5 መቶ ሺህ ብር በላይ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ማቀዱን ገልፀዋል፡፡ በተያዘው እሩብ በጀት ዓመት 3 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር ብድር ማሰራጨቱንና መቶ ሺህ ብር ቁጠባ መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመው 6 ሺህ 8 መቶ የሚሆኑ የህብረተሰቡ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል ሲል ሪፖርተር አካሉ ጥላሁን ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል፡፡

Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia

Appeal to:- Mr. Ban Ki -Moon, United Nation’s Secretary General, United Nations, 760 United Nations Plaza Manhattan, NY 10017, USA Mr. José Manuel Barroso President of the European Commission 1049 Brussels, Belgium Mrs. Inkosazana Dlamini Zuma, African Union’s Secretary General P.O. Box 3243 Roosvelt Street (Old Airport Area) W21K19 Addis Ababa, Ethiopia Secretary Hillary Rodham Clinton The US Department of State 2201 C Street Northwest Washington, DC, USA 20 November 2012 Subject: - Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia The Sidama people live in Southern Ethiopia. According to the Ethiopian Government’s official statistics, the current population of Sidama is 3.4 million (independent estimates suggest that the current total population is above 5 million). The Sidama nation had a long history, vibrant culture and democratic systems of governance based on traditional Kingships and various democratically elected traditional councils of elders. This traditional system of go

የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ለመገንባት 63 ሺህ በላይ ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን የሀዋሣ ከተማ ጤና መምሪያ ገለፀ፡፡መምሪያው የ2ዐዐ5ሩብዓመትእቅድክንውንገምግሟል፡፡

Image
የእቅድ ክንውን ሪፖርት በቀረበበት ወቀት የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደሰታ ዶጊሶ አንደተናገሩት በሩብ አመቱ የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የጤናና የማህበራዊ ችግሮች በመፈታት ነዋሪውን ጤናማ፣ አምራችና የበለፀገ ለማድረግ የጤና ልማት ሰራዊት ግንባታ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ከመገንባት አንፃርም ከ63 ሺህ 993 ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን ተናግረዋል፡፡ በሪፖርቱ እንደቀረበው የሳንባ ነቀርሳ በሽታን መከላከያ ክትባት ለ2 ሺህ 678 ህፃናት ለመስጠት ታቅዶ 2 ሺህ 971 የተከናወነ ሲሆን ባለፈው ሩብ አመት አብዛኛዎቹ አፈፃፀሞች ከእቅዱ 9ዐ በመቶ እና ከዚያ በላይ ተግባራዊ መሆናቸው በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡ ከመንጋጋ ቆልፍ በሽታ የተጠበቀ ህፃናት እንዲወለዱ ከማድረግ አንፃርም በሩብ አመቱ 2 ሺህ 678 ህፃናት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ መከናወኑንም ተጠቁሟል፡፡ በመቀጠልም በበጀት ዓመቱ የጤና ሴክተር ትኩረት የሚያደርገው የጤና ተቋማት በማስፋፋትና በግብዓት በሟሟላት የጤና አገልግሎቶች ጥረት ማሻሻል የእናቶችና የህፃናት ሞትን በመቀነስና ዋና ዋና ተላላፊ በሽታዎችና መከላከልና መቆጣጠር ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነት 124 እናቶች የወሊድ አገልግሎት ለመስጠት እቅድ ተይዞ ለ49 እናቶች ብቻ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በተሻለ ሁኔታ ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡ በምክክር መድረኩም የሀዋሣ ክፍለ ከተሞች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/1

የህፃናት መብቶችን በተመለከተ ከጊዜ ወደ ጊዜ የህብረተሰቡ ግንዛቤ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ሠብአዊ መብት ኮሚሽን ሀዋሣ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ጽህፈት ቤቱ 7ኛውን የአለም ህፃናት ቀን ከትምህርት ቤቶች ጋር አክብ b ል፡፡ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃ አታሮ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ሰብአዊ መብትን በተመለከተ ህፃናት ተኮትኩተው የሚያድጉበት በመሆኑ የኮሚሽኑን አላማ ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡ መጪው ትውልድ ሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችለውን ስንቅ ከትምህርት ቤቶች ይቀስማል ብለዋል ፡፡ በሀገራችን ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ህፃናት ቀን “ሁሉም ህፃናት ሰብአዊ መብቶችን በማከበር፣ በማስከበርና ሌሎችንም በማስገንዘብ ትምህርት ቤቶች ትልቅ ሚና አላቸው” የሚል መርህ አላው፡፡ በበአሉ አለም አቀፍ የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽንን፣ የአፍሪካ ህፃናት ሰብአዊ መብትንና የኢትዮጵያ መንግስት ለሠብአዊ መብቶች የሠጠውን ትኩረት የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡ የበአሉ ተሳታፊ ህፃናቶች የተለያዩ ጭውውቶችንና ሥነ ጽሑፎችን አቅርበዋል፡፡ ትምህርት ቤቶች በሥነ ምግባር የታነፀ የሞራል እሴት ያለው፣ የነቃና ህግ አስከባሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት  ህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል ፡፡ ባለደረባችን ደስታ ወ/ሰንበት እንደዘገበው፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN305.html

ከመፈክር ይልቅ ዲሞክራሲ!

ሰላም! ሰላም! ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ላላችሁ በሙሉ። አንድ ወዳጄ ይኼንን የአቅጣጫ ሰላምታ እንደማይወደው አጫውቻችሁ አውቃለሁ? ለምንድን ነው ስለው ‹‹የሰው ልጅ እንደ ንፋስ በአቅጣጫ ላይ ተመሥርቶ ሰላምታ ሲለዋወጥ እበሽቃለሁ፤›› አይለኝ መሰላችሁ? የዘንድሮን ሰው የሚያበሽቀውን ነገር ብዛት ቆጥረን መጨረስ አቃተን! ግን ግን ንፋስን ለምንከተል የዘመኑ ሰዎች ይህ ሰላምታ ካልተሰጠ ለማን ይሰጥ? ለራስ ብቻ የሚሮጥበት ዘመን መሆኑን ካየን ዘንዳ ከዚህ ሌላ ምን ይባላል? አንዳችን ያለ ሌላችን መኖር እንደማንችል እያወቅነው ‘እኔ’ን ብቻ ላማከለ ነፍስ መሮጣችን ይገርመኛል። የሚገርማችሁ ደግሞ አባባልን እንኳ መርጠን አለመጠቀማችን ነው። ለምሳሌ ‹‹ዘመኑ የውድድር ነው›› የሚለውን አባባል ለተቀደሰ ይሁን ለረከሰ ተግባር እንደምንጠቀምበት ሳንለይ ለሁለቱም እንዳሻን እንገለገልበታለን። አሁንማ ሙሰኛውም በሰሞነኛ ተቆጣጣሪዎች ሲያላግጥ ‘ዘመኑ የውድድር ነው’ ማለት ጀምሯል አሉ። ‹‹ውድድሩ ጤናማ ዕድገት ለማስመዝገብ ነው? ወይስ እንደተለመደው ጠልፎ ለመጣል ነው?›› ይሉኝ ነበር ባሻዬ ይኼን ጉድ ቢሰሙ፡፡ ሌባ ቀጪ አጥቶ ለሕዝብ አገልግሎት በሚውል ገንዘብ ደልቦ ሲንጎማለል ይውላል። ተጠቂው ሰፊው ሕዝብ አቧራ ለብሶ ለዕለት ጉርሱ ይማስናል። ፍትሕ የናፈቃት ዓለም። በየጥጋጥጉ ዲስኩር ብቻ ተለጥፎ ይነበባል! ይነበነባል! የባሻዬ ልጅ፣ ‹‹አሁንማ የሰለቸኝ መፈክር ማንበብ ነው፤›› አለኝ፡፡ ‹‹ለምን?›› ብለው፣ ‹‹በመፈክር ውስጥ የተሸጎጡ በርካታ ውሸቶች አሉ፤›› ሲለኝ የገዛ ሳቄ ጆሮዬን አደነቆረው፡፡ ባለፈው ሰሞን አንድ የመንደራችን ጎበዝ ተማሪ ‹‹እኔ ከእንግዲህ ወዲያ ትምህርት የሚባል በቃኝ አቅለሸለሸኝ፤›› ብሎ አቆመው

ድብልቅልቅ ስሜቶችን የፈጠረው የኢትዮጵያ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልነት

Image
በዮሐንስ አንበርብር ሰሞኑን ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች 18 አገሮችን በሥሩ ለሚገኘው የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባል አድርጐ መርጧል፡፡ ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ አባል ሆና መመረጧ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አስደንቋል፤ አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የኢትዮጵያን አባል መሆን በአገሪቱ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያላገናዘበ ሲሉ ተችተውታል፡፡ በሌላ በኩል የውጭ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች አጋጣሚውን የወደዱት ቢመስልም የሰብዓዊ መብት ወቀሳቸው ግን ቀጥሏል፡፡ የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ባለፈው ሳምንት ባካሄደው ምርጫ 47 መቀመጫዎች ላሉት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤቱ 18 አባል አገሮችን በተተኪ አባልነት ለቀጣይ ሦስት ዓመታት እንዲያገለግሉ መምረጡን ይፋ አድርጓል፡፡ የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ የ193 አባል አገሮችን ድምፅ የያዘ ሲሆን፣ በሰብዓዊ መብቶች ካውንስል ውስጥ አባል ለመሆን ከ96 በላይ የሚሆኑ አባል አገሮችን ይሁንታ ማግኘት ይጠይቃል፡፡ ባለፈው ሳምንት በተካሄደው ምርጫ ከኢትዮጵያ ጋር ሌሎች ስድስት የአፍሪካ አገሮችም ተመርጠዋል፡፡ እነዚህ የአፍሪካ አገሮች ያገኙት ድምፅ የተሻለ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ከ193 የጠቅላላ ጉባዔው አባላት ድምፅ የ178 አገሮችን ይሁንታ በማግኘት ምክር ቤቱን በአባልነት ተቀላቅላለች፡፡ ለሰብዓዊ መብቶች  መከበር የፀና እምነት መኖርና ለተግባራዊነታቸው መንቀሳቀስ፣ የተሻለ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝና ለዚህ የሚሠሩ ጠንካራ ተቋማት መኖር የምክር ቤቱ አባል ሆኖ ለመመረጥ ከሚያበቁ ዋነኛ መስፈርቶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲፈጠር በመላው የዓለም አገሮች ውስጥ የሚሠራ ነው፡፡ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓ

ሲዳማ ቡና ቅጣት ተላለፈበት

Image
•ፕሪሚየር ሊጉ ነገና ከነገ በስቲያ ቀጥሎ ይካሄዳል ሲዳማ ቡና እየተካሄደ በሚገኘው የ2005ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መለስ ዋንጫ ውድድር በአራተኛው ሣምንት ሲዳማ ቡና በሜዳው ይርጋለም ላይ አርባ ምንጭ ከነማን ባስተናገደበት ጨዋታ በተፈጠረው የዲሲፕሊን ጥሰት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቅጣት ተላልፎበታል። ፌዴሬሽኑ ያደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው ውድድሩን የሚመራው የሊግ ኮሚቴ ከዲሲፕሊን ኮሚቴ የደረሰውን ሪፖርት ከገመገመ በኋላ ሲዳማ ቡና በስድስተኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ነገ በሜዳው ከሃዋሳ ጋር ሊያደርግ የነበረውን ጨዋታ በሌላ ገለልተኛ ሜዳ እንዲያካሂድ ወስኖበታል። ይህንንም ተከትሎ ሁለቱ ቡድኖች ይርጋለም ላይ ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ የቦታና ሰዓት ለውጥ ተደርጎበት በአሰላ ስታዲየም ከቀኑ በስምንት ሰዓት የሚካሄድ ይሆናል። ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጪ የሆኑ ተግባራት የተመልካቾች ማነስ እያሳሰበው ለሚገኘው የዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መለስ ዋንጫን የበለጠ የሚያደበዝዙት በመሆኑ ክለቦች ደጋፊዎቻቸውንም ሆነ ተጫዋቾቻቸውን ለስፖርታዊ ጨዋነት መርሆዎች ተገዢ እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። የስድስተኛው ሣምንት የፕሪሚየር ሊጉ ውድድር ነገና ከነገ በስቲያ ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን፤ ሰባት ጨዋታዎችም ይከናወናሉ። አምስቱ ጨዋታዎች ነገ በአበበ ቢቂላና በክልል ከተሞች የሚደረጉ ሲሆን፤ ሁለቱ ደግሞ ሐሙስ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይደረጋሉ። በእዚሁ መሠረት ነገ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል ኢትዮጵያ ቡና ከመከላከያ የሚያደርጉት ጨዋታ ትልቅ ትኩረት ስቧል። ሁለቱ ክለቦች በደረጃ ሠንጠረዡ በአንድ ነጥብ ተበላልጠው ስምንተኛና ዘጠንኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ መከላከያ በሰባት ነጥብ ስምንተኛ እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና

የክልሉ መንግስት በሁሉም አካባቢዎች ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍልና የመሠረተ ልማት ዝርጋታን ለማረጋገጥ እየሠራ መሆኑን የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ አስታወቁ፡፡

Image
ከአራት የአውሮፖ አገራት ፓርላማዎች የተውጣጡ ልዑካን ቡድን አባላት በክልሉ በአውሮፖ ህብረት ድጋፍ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ውጤታማ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ አባላት ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፣ም/ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊና ከክልሉ ምክር ቤት ኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር መክረዋል፡፡ ዝርዝሩ የደቡብ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ነው፡፡ በአውሮፖ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የልማት ኘሮጀክቶችን እንስቃሴ ለማየት ከሀንጋሪ፣ ክቼክ ሪፓብሊክ ፣ ከሶሎቫኪያና ከፖላንድ ፓርላማዎች የተወከሉና የልማት ድርጅቶች ተወካዮች ጉብኝት እያደረጉ ናቸው፡፡ የልዑካኑ ቡድን አባላት ከደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በወቅቱ ርዕሰ መሰተዳድሩ እንዳሉት የክልሉ መንግስት በሁሉም የልማት ዘርፎች የክልሉን አካባቢዎች እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ ነው፡፡ ባለፉት አመታት በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌያት የህፃናትን ሞትን ለመቀነስ ተችሏል፡፡ ከ6ዐዐ በላይ ጤና ጣቢያዎችም ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ ናቸው፡፡ አርሶ አደሩ በቂ ምርት እንዲያመርትና ራሱን ከመመገብ አልፎ ለገበያ እንዲያቀርብ የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑን አቶ ሽፈራው ተናግረዋል፡፡ በሀገሪቱ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት የሚያሰችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸሉ ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በ2ዐዐ5 ዓ/ም 65ዐ ሚሊዮን ብር በመመደብ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ እየተሠራ ያለውን ለአብነት አንስተዋል፡፡ በቼክ ሪፓብሊክ ኤምባሲ የልማት ተልዕኮው ምክትል ኃላፊ ሚስስ ጃና ኮርቤሎቫ እንዳሉት በክልሉ የሚደረጉ የልማት ሥራዎች ውጤታማ ናቸው፡፡ እነዚህን በ9 ወረዳዎች በግብርና፣ በትምህርት

የህዳሴ ግድብ በተያለዘት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት መወሰናቸውን የወንዶ ገነት ወረዳ የወጣቶችና የሴቶች ሊግ ገለፀ፡፡

የ2ዐዐ4 ዓ/ም የስራ ክንውን በመገምገም በተያዘው የበጀት አመት አበይት የትኩረት አቅጣጫዎችን ለይተው ተቀናጅተው ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ ለአንድ ቀን ባካሄዱት የወጣቶችና ሴቶች ሊግ የጋራ ስብሰባ ባለፈው አመት ባከናወኗቸውና በቀጣይ በሚሰ b ቸው አበይት ስራዎችን ለአባላቱ በማቅረብ ተወያይተውበታል፡፡ በዚህም የወጣቶች ሊግ በተጠናቀቀው አመት በከተማ የስራ አጥነት ችግር በቁጠባ፣ በአካባቢ ፅዳት ስራዎች የበጎ አገልግሎት ላይ ወጣቶች በስፋት እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ በገጠር ወረዳው ያለውን ምቹ የመሰኖ አቅምን  በዘመናዊ መንገድ እንዲጠቀሙ ግንዛቤ መፍጠር መቻላቸውን የወረዳው ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሴ ሙዴ ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይ የወረዳው ሴቶች ሊግ ጽህፈት ቤት ኃለፊ ወይዘሮ ድንቅነሽ ደግፌ እንዳሉት የወረዳው ሴቶች በተለይም የገጠር ሴቶች በሰብልና በእንስሳት ሀብት ዘርፍ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ እንዲሁኑ ስራዎችን በመስራት ምርታማ ለማድረግ ተንቀሳቅሰናል ይላሉ፡፡ የሁለቱ ሊጐች አባላት በተደረገ ውይይትም የ2ዐዐ5 የትኩረት አቅጣጫ ላይ ከመግባበት የደረሱ ሲሆን በጋራ ሆነው የተጀመሩ ስራዎች ቀጥሏል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የህዳሴው ግድብ በተያለዘት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከወጣቶችና ሴቶች ሊግ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት መወሰናቸውን አቶ ሙሴ ተናግረዋል፡፡ ሌላው ትልቁተግባራቸውም በቀጣይ በሚከናወነው ማሟያ ምርጫ ላይ እነዚህ አካላት ከዚህ ቀደም ከከነበራቸው ተሳትፎ በላቀ ደረጃ እንደሚሳተፉ ም ተስማሟተዋል፡፡ የወረዳው ዴህዴን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኤርሚያስ ደበላ በበኩላቸው ሊጐቹ ለወጣቶችና ሴቶች ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው በማሳሰብ በቀጣይ ደካማ አፈፃፀማቸውን በማረም ጠንካራ ጎናቸውን በማጠናከር መ

የቡና ምርት መጠንና ጥራትን በማስጠበቅ በአለም ገበያ ተወዳዳሪ ለማድረግ በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው የባለ ድርሻ አካላት ግብረ ኃይል ፎረም ስብሰባ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ክቡር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ እንዳሉት የቡና ግብይት ስርዓቱ ውጤታማ በማድረግ የአርሶ አደሩን ገቢና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡

ባለፉት ተከታታይ የምርት ዘመናት በተደረገ ሰፊ እንቅስቃሴ በቡና ምርት ዝግጅት ስራ ላይ የነበሩ ድክመቶችን ለይቶ በማስወገድ ረገድ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋልም ብለዋል፡፡ ዘመናዊ የግብይት ስርዓቱን ጤናማ በማድረግ ሀገሪቷ ከዘርፉ የምታገኘው የገቢ እቅድ ለማሳካት ምርቱን በወቅቱ ያለማቅረብና ህገወጥ የቡና ግብይቶች የመሳሰሉ ችግሮች ለማስወገድ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው እንዲንቀሳቀሱም አሳስበዋል፡፡ የቡና ግብይ ማዕከላትን በማጠናከር የቡና ጥራትና ንግድ ቁጥጥሩ በአስተባባሪ ግብረ ኃይሎች ሊጠናከር ይገባልም ብለዋል፡፡ የንግድ ሚኒስቴር ማኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ እንዳሉተም የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተነድፎ ተግባራዊ መሆን ከተጀመረ ወዲህ ሀገሪቷ ከውጭ ምርቶች የሚገኘው ገቢ እያደገ መጥቷል፡፡ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መጨረሻ ሀገሪቷ ከውጭ ምርቷ የምታገኘው ገቢ 1ዐ ነጥብ አራት ቢሉዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት ሚኒስትሩ በያዝነው ዐመት 5 ቢልዮን ዶላር ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የቡ ምርቱ መጠንና ጥራት በማሻሻልም ዘንድሮ ከአንድ ነጥብ አነድ ቢልዮን ዶላር በላይ ገቡ እንዲገኝ የታቀደውን ዕቅድ ለማሳካት ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል፡፡ ከአምራቾች እስከ ገበያ ድረስ ያለው የጥራትና የአቅርቦት ችግሮች በማስወገድ በያዝነው የምርት ዘመን 3መቶ 43 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም አሳስበዋል፡፡ በውይይቱ የቡና ምርት መጠንና ጥራት እንዲሁም የግብይት ስርዓቱ እየተሻሻለ ቢመጣም ወደፊት የተሻለ ዋጋ ሊያወጣ ይችላል በሚል ቡናን አከማችቶ ያለመሸጥ ችግር፣ ህገወጥ ግብይት ሙሉ በሙሉ አለመወገድ፣ የመጀመሪያ የቡና ግብይት ማዕከላት አለመጠናከርና፣ የብድር አቅርቦት ችግሮ

Unity over Rights Pave Ethiopian Oppositions’ Future

Image
It takes two to tango. EPRDF’s talk about democracy appears to deal more with the image of democracy than with its reality. The oppositions’ talk about democracy seems to be targeted more at assuming power by whatever means than at providing a unified alternative for the people to choose from. That is the drama of democracy played everyday inEthiopia. The vital question, however, is; how can the drama be abandoned and reality be adopted? Standing at the fore of the stage is the Ethiopian opposition. How the drama would be played out would also be highly dependent on their move. The political climate on the ground is squeezing the opposition with each passing day. To make things worse, the opposition itself is weak due to divisions. Forgoing its purpose, it settles for mere opposition. The opposition has to go through rebirth. Otherwise, it will soon become a do-nothing force as far as peaceful struggle is concerned. Even then, the opposition is not at the mercy of the