Posts

Showing posts from April, 2012

Coffee processing in Sidama, Ethiopia

Image
http://www.firstpost.com/topic/place/vietnam-coffee-processing-in-sidama-ethiopia-video-Z6dCWkYVNpw-270-7.html

በሀዋሣ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ መሠረታዊ ማህበራት ከ9 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ መቻላቸው ተገለፀ::

Image
በሀዋሣ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ መሠረታዊ ማህበራት ከ9 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ መቻላቸው ተገለፀ::የወረዳው የግብይትና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት እንዳለው በ23 ቀበሌያት የተቋቋሙት ማህበራት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማቱን በማገዝ በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው:: የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ማርቆስ ማህበራቱ በሁለገብ መሠረታዊ ህብረት ስራ፣ በወጣት፣ በገንዘብ ቁጠባና ብድር እንዲሁም በወተትና የወተት ተዋፅኦ፣ በኃይድሮ ኤሌክትሪክና ሶላር ማህበራት የተቋቋሙ መሆናቸውን ተናግረዋል::መስኖ፣ ማዕድንና የደን ልማት ቀሪዎቹ ማህበራቱ የተደራጁባቸው መስኮች መሆናቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል:: የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መኮንን ወላንሳ በበኩላቸው ህብረት ስራ ማህበራት የነበሩባቸውን የአመለካከትና ግንዛቤ ችግር ቀርፈው ችግር ፈቺ እየሆኑ መምጣታቸውን መናገራቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN104.html

በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ 16ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች ተግባራዊ ያደረጉ 228 አባወራዎችና እማወራዎች ማስመረቁን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ::

Image
በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ 16ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆች ተግባራዊ ያደረጉ 228 አባወራዎችና እማወራዎች ማስመረቁን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ::የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታደሰ አኔቦ አንዳሉት በጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም የግልና የአካባቢ ንጽህናን፣ የቤተሰብ ጤና ክብካቤንና የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር በቤተሰብ ደረጃ እውን እንዲሆን መጠነ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል:: ርብርቡን ስኬታማ ለማድረግም በወረዳው የዛሬዎቹን ጨምሮ 38 ሺህ 459 አባወራና እማወራዎች መሰልጠናቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል::የዞኑ ጤና መምሪያ መከላከልና ጤና ማጎልበት ኦፊሰር አቶ ኢማላ ላሚቻ በበኩላቸው መንግስት የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የነደፈውን የጤና ፖሊሲ ስኬታማ ማድረግ ከተመራቂዎች የሚጠበቅ ተግባር ነው ማለታቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN304.html

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተያዘው የምርት ዘመን ከ171 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ::

Image
በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተያዘው የምርት ዘመን ከ171 ሺህ  ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ:: የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ ጋቤራ ለወረዳው ምክር ቤት 3ኛ ዙር 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ባቀረቡት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ምርቱ የተሰበሰበው በ6 ሺህ 5 መቶ 9ዐ ሄክታር መሬት ላይ ከተመረቱ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ቦሎቄና ከሌሎች ሰብሎች መሆኑን ገልፀዋል::በምርት ዘመኑ 625 ሺህ የቡና ችግኞች ለበልግ የተከላ ወቅት መዘጋጀታቸውን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው በ156 ሄክታር መሬት ላይ የነበሩ ያረጁ የቡና ተክሎች ተጐንድለዋል::2ዐ ኩንታል የቡና ዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል:: በወረዳው የተሻሻሉ ምርጥ የከብት ዝሪያዎችን ለማርባት 82 ከብቶች በሰው ሠራሽ ዘዴ፣ 447 ደግሞ በኮርማ መዳቀላቸውን አውስተው የእንስሳት በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል በተደረገው ጥረት ለ6 መቶ ከብቶች ክትባት መሰጠቱን ገለፀዋል::ሪፖርተራችን ካሳ ጀንቦላ ከበንሳ ቅርንጫፍ እንደዘገበው:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN604.html

በሀዋሣ ታቦር ክፍለ ከተማ የፋራ ቀበሌ አስተዳደር የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት የምሳ ግብዣ አደረገ:

በሀዋሣ ታቦር ክፍለ ከተማ የፋራ ቀበሌ አስተዳደር የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት የምሳ ግብዣ አደረገ::የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ አቶ በልጉዳ ባሪሳ በዝግጅቱ ላይ እንዳሉት የሁላችንም የጋራ ጠላት የሆነውን ድህነትና ኃላቀርነትን ለማሸነፍ በተሰማራንበት መስክ የበኩላችንን ድርሻ ልንወጣ ይገባል::በቀበሌው ከ47ዐ በላይ አረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት ለምሳ ግብዣው በመጥራት በአሉን በጋራ ማክበር መቻላቸውን አስረድተዋል:: ድጋፍ ያደረጉ ባለሀብቶች በበኩላቸው አመት በዓልን ጠብቆ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት ከሚደረገው ድጋፍ ባሻገር በዘላቂነት ህይወታቸውን ለመቀየር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል::የሀዋሣ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ተዋካይ አቶ አየለ ኪአ ቀበሌው እንደዚህ አይነት ዝግጅት በራሱ ተነሳሽነት ማካሄዱ የሚያመሰግነው መሆኑን ገልፀው፤ ሌሎችም አርአያነቱን ሊከተሉ እንደሚገባ አውስተዋል:: የፋራ ቀበሌ ከአመት በዓል ዝግጅቶች ባለፈ የችግረኛ ወገኖችን  ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ስራ እየሰራ መሆኑን ተገልጿል ሲል ባልደረባችን ወንድወሰን ሽመልስ ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN704.html

የሀዋሣ ግብርና ምርመር ማዕከል አዳዲስ የአኩሪ አተርና የባቄላ ዝርያዎችን መልቀቁን አስታወቀ::

የሀዋሣ  ግብርና ምርመር ማዕከል አዳዲስ የአኩሪ አተርና የባቄላ ዝርያዎችን መልቀቁን አስታወቀ::በብሔራዊ የዝሪያዎች አፅዳቂ ኮሚቴ ተገምግሞ የፀደቀው ሁለት የአኩሪ አተርና አንድ የባቄላ ዝርያዎች ሲሆን አስካሁን ከተለቀቁት ከ16 እስከ 21 ቀናት በመቅደም የሚደርሱ ናቸው::ዝርያዎቹ በተዘሩ በአማካኝ ዘጠኝ ቀናት ውስጥ የሚደርሱ ናቸው:: በሽታን የመቋቋም አቅማቸው ከፍተኛ ሲሆን ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ጭምር ማምራት እንደሚቻል ተገልጿል::ግኝቱ ለአርሶ አደሩ አዋጭ ከመሆኑም በተጨማሪ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግም ከምርምር ማዕከሉ የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN904.html

Agricultural Cooperatives and Rural Livelihoods: Evidence from Sidama Ethiopia

Agricultural Cooperatives and Rural Livelihoods: Evidence from Ethiopia Kindie Getnet  affiliation not provided to SSRN Tsegaye ANULLO  affiliation not provided to SSRN Annals of Public and Cooperative Economics, Vol. 83, Issue 2, pp. 181-198, 2012   Abstract:       ABSTRACT:  Agricultural cooperatives are important rural organizations supporting livelihood development and poverty reduction. In recognition of such roles of cooperatives, Ethiopia showed a renewed interest in recent years in promoting cooperative sector development. However, there is lack of a wider and systematic analysis to produce sufficient empirical evidence on the livelihood development and poverty reduction impacts of cooperatives in the country. Using a matching technique on rural household income, saving, agricultural input expenditure and asset accumulation as indicator variables, this paper evaluates the livelihood impact of agricultural cooperatives in  Sidama  zone, Ethiopia. The finding shows tha

Wednesday, April 25, 2012 Colorado State University Signs International Memorandum with Ethiopia's Hawassa University - News & Information - Colorado State University

Image
FORT COLLINS  - Colorado State University signed an international Memorandum of Understanding (MOU) with Ethiopia’s Hawassa University to provide collaborative research and teaching opportunities for faculty and graduate students at the two universities. The MOU was signed in January of this year, and in February, a team of four CSU researchers from the Natural Resource Ecology Laboratory traveled to south-central Ethiopia where they taught short courses in geographic information systems, watershed management, animal nutrition and forest ecology at the Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources located off Hawassa’s main campus. Additionally, the team visited potential research sites and met with Hawassa faculty and Peace Corps volunteers. “Hawassa University is very similar to CSU in that both universities are about the same size and offer similar programs, including a veterinary school and a college of natural resources,” said Dave Swift, senior research sc

በሀዋሳ የጎብኚዎች ቁጥርና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እየጨመረ ነው

Image
ሃዋሳ, ሚያዝያ 16 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - ዜና ትንታኔ በደቡብ ኢትዮጵያ ሰምጥ ሸለቆ የምትገኘው ሀዋሳ ለቱሪስቶች ምቹና ተመራጭ ከተማ እየሆነች መምጣቷን የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎቿና አስተናጋጆቿ ይናገራሉ፡፡ በቅርቡ ሀዋሳ ከተማ ጎራ ብለው የቆዩት ቻይናዊው ሚስተር ጆ ጂን እና ኬንያዊው ሚስተር ኒልሰን ቴምሊ የሀዋሳ ሃይቅ፣የአካባቢው የተፈጥሮና መልከአድራዊ አቀማመጥ፣ሀይቁ ዳር የሚገኘው የሌዊ ሪዞርትና መዝናኛ ፣የህዝቡ እንግዳ አቀባበል ስርአት እንደተመቻቸውና እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡ የከተማው ንጽህናና ውበት፣በመገንባት ላይ ያሉ አዳዲስ ህንፃዎች ፣ምቹ የመናፈሻ ቦታዎችን ጨምሮ ሀዋሳ ለኑሮ ተስማሚ በመሆኗ ወደፊትም የመዝናኛ ምርጫቸው እንደሆነች ተናግረዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ለመዝናናት ወደ አዋሳ ያቀኑት አቶ ኩቲ ኢታይ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ማረፊያቸውን ሌዊ ሪዞርት በማድረግ የሀዋሳ ሃይቅ ላይ በዘመናዊ ፈጣን የጀልባ ሽርሽር አሳን በማስገር እንዲሁም የሆቴሉ መስተንግዶና አገልገሎት ምቹ በመሆኑ ትዳር ሲይዙ እዚሁ ለማሳለፍ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማውና አካባቢው ያሉት ተፈጥሮአዊ ታሪካዊና ባህላዊ መስህቦች ለመጎብኘት የሚመጣው የቱሪስት ፍሰትና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱን የሚገልጹት የከተማው ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የመረጃና ፕሮሞሽን ባለሙያ ወይዘሮ እታፈራሁ ተምትም ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 97 ሺህ 187 የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ተስተናግደው ከ22 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ፡፡ ከጎብኚዎቹም መካከል ከ21 ሺህ በላይ የውጭ ቱሪስቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በጎብኚዎች ብዛ

Over 153,000 People Receive VCT Service in Sidama

Hawassa, 14 April 2012 (allAfrica)  — More than 153,  people  have received HIV and AIDS Voluntary Counseling and blood Testing (VCT) in Sidama Zone over the past seven months, the zonal health department said. Health Promotion and Disease Preventions Process owner coordinator Yohannes Latamo told ENA that more than 80,000 of them are women. He said the department is working with government and NGOs to expand VCT service to reach out more community. Some 520 people have found to be positive, he said. Following the establishment of HIV and AIDS fund in government offices care and support service is being offered to 39 people living with HIV and AIDS, he said. He said government offices have also allocated two percent of their budget each for HIV and AIDS prevention and control activities. With this fund, 21 people living with HIV and AIDS are taking Anti-Retroviral Treatment and more than 5,000 orphaned and vulnerable children are provided shelter, food and  educational m

የሃዋሳ ስታዲዬም በ548 ሚሊዮን ብር ወጪ የግንባታ ስራው ተጀመረ

የደቡብ ክልል መንግሥት ነዋሪዎቹ ለሕዳሴው ግድብ ግንባታ ገንዘብ እያዋጡ በመሆኑ ላለማስጨነቅ ሲል በራሱ ወጭ የአዲስ ስታዲየም ግንባታ አስጀመረ፡፡ ክልሉ ለስታዲየሙና ለተያያዥ ግንባታዎች ትናንት ሐሙስ ሚያዝያ 11 ቀን 2004 ዓ.ም. ሳትኮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ በ548 ሚሊዮን ብር እንዲገነባለት ውል ተፈራርሟል፡፡ ከዚህ በጀት ውስጥ 80 ሚሊዮኑን በዚህ የበጀት ዓመት ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ሲሆን፣ ይህንን ጨምሮ በ2005 በጀት ዓመትም ለሥራው የሚያስፈልገውን ገንዘብ የሚመድበው ክልሉ ነው፡፡ ይህ የተወሰነው ሐዋሳ ከተማ ላይ ስታዲየሙን ጨምሮ የሚገነባውን ግዙፍ የስፖርት ኮምፕሌክስ እንዲያሠራ የተሰየመው ምክር ቤት ከክልሉ መንግሥት ጋር ከመከረ በኋላ መሆኑ ታውቋል፡፡ የስፖርት ኮምፕሌክስ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበርያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰፋ አመሎ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በ2004 እና በ2005 በጀት ዓመት ክልሉ ከራሱ ካዝና እየመደበ ያሠራል፡፡ በ2006 በጀት ዓመት ሕዝብ ለግንባታው አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ይጠይቃል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ሥራውን ሐሙስ ተረክቦ በዕለቱ ቁፋሮ የጀመረው ሳትኮን ኮንስትራክሽን ይህንን ፕሮጀክት ለማሸነፍ ከስምንት ኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሯል፡፡ ከስምንቱ ውስጥ ሦስቱ በቴክኒካል ጨረታ ሲወድቁ፣ አምስቱ ጨረታውን አልፈው በፋይናንስ ጨረታ ተወዳድረዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች ውስጥ ሳትኮንን ጨምሮ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን፣ ሚድሮክ ኮንስትራክሽንና ቫርኔሮ ይገኙበታል፡፡ ከአምስቱ የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ውስጥ ዝቅተኛውን 548 ሚሊዮን ብር ለመጀመርያው ዙር የስታዲዮም ግንባታ በማቅረብ ሳትኮን አሸንፏል፡፡ ከፍተኛ የሆነውን የጨረታ ገንዘብ 564 ሚሊዮን ብር ያቀረበው ቫርኔሮ ሲሆን፣ ሦስቱ ኮንስትራክሽን

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ:

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ::በሀዋሣ ከተማ የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከፍተኛ ሁለት ዐ3 ቀበሌ መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ከሳውዲን ተራድኦ ድርጅት ኘሮጀክት ጋር በመተባበር ለ145 ወላጅ አጥና ችግረኛ ህፃናት የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል:: የኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሣ ቅርንጫፍ ሥራ አስያኪጅ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት ህፃናቱ ቀደም ሲል የትምህርት ፣ የጤናና የስነ ልቦና ድጋፍ ሲሰጣቸው የቆዩ ናቸው::ከፍተኛ ሁለት ዐ3 መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከድርጅታቸው ጋር በመተባበር የሚያደርግላቸውን ድጋፍ በመጠቀም ህፃናቱ በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል:: የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ ወይዘሮ ዘውዲቱ ገ/መስቀል በበኩላቸው የመረዳጃ እድርና ልማት ማህበሩ ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመተባበር  በክፍለ ከተማው በዓላትን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለወላጅ አጥና ችግርተኛ ህፃናት የተለያዩ ድርጋፎችን  እንደሚያደርግ ተናግረዋል:: የአሁኑ ተረጂ ህፃናት በሚደረግላቸው ድጋፍ ተግተው ከተማሩ የነገይቱ አገር ተረካቢና የተሻለ ዜና መሆን እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡ ባልደረባችን ጌታሁን አንጭሶ እንደዘገበው::

Hawassa constructing 40 mln. Birr worth cultural centre

Image
Hawassa, April 21, 2012 (Hawassa) - Construction of a multi-purpose hall cultural centre is underway in Hawassa town of South Ethiopia Peoples State at a cost of close to 40 million Birr, the town municipality said. Municipality deputy manager, Biru Wolde told ENA that the center, which would be finalized in the next Ethiopian budget year would accommodate 1,700 guests at a time. He said the centre which houses conference hall, theater and art gallery, among others would help conserve historical and cultural heritages of the region. The construction has created dozens of jobs. The regional government and the municipality have covered the construction cost of the centre.

Sidama Libration Front -የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

Image
Seife Nebelbal Radio, April 20, 2012, Interview: Asli Oromo and Sidama Liberation leader Kaala Betana የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር  የተደረገ ቃለ ምልልስ ከ 24 ደቂቃ ጀምረው ያዳምጡ::

መድኃኒትና ንብረት የዘረፉ ክስ ተመሠረተባቸው

Image
ፈንድ አቅርቦት ኤጀንሲ የሃዋሳ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ የነበረው ግለሰብና ሌሎች ስድስት ግለሰቦች በመመሳጠር ከኤጀንሲው የመድኃኒት ማቆያ መጋዘን ውስጥ ከ1ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መድኃኒት በመዝረፍ በከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ተከሰሱ። የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በግለሰቦቹ ላይ የመሠረተው ክስ እንደሚያመለክተው የኤጀንሲው የጥበቃ ሠራተኛ የነበረ 1ኛ ተከሳሽ የመንግሥትን ንብረት እንዲጠብቅ የተሰጠውን ኃላፊነት ወደጎን በመተው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራሱ እና ለግብረ አበሮቹ ለማስገኘት በማሰብ ለሕዝብ አገልግሎት ይውሉ የነበሩትን መድኃኒቶች፣ ኬሚካሎች፣ የሕክምና መሣሪያዎች እንዲዘረፉ በማድረጉ ከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ፈጽሟል። የኤጀንሲው ሠራተኞች ያልሆኑት ከ2ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተከሳሾች ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር ተመሳጥረው መድኃኒት የተከማቸበትን መጋዘን ቁልፍ በመስበር መድኃኒቱ የሚጫንበትን ተሽከርካሪ በማዘጋጀት መድኃኒቱን ከመጋዘን አውጥተው በመጫን እንዲሁም መድኃኒቱ የሚራገፍበትን ቦታ በማመቻቸት በወንጀሉ ድርጊት ሙሉ ተሳታፊና በወንጀሉ የተገኘውን ውጤት ተካፋይ መሆናቸውን የክስ መዝገቡ ያስረዳል። 7ኛ ተከሳሽ የሆነው የኤጀንሲው የጥበቃ ተከሳሽ ዘረፋው በተፈጸመበት ዕለት ተረኝነቱን ሳይጠብቅና የሙያ ግዴታውን በአግባቡ ሳይፈጽም ሌሊቱን ጥበቃ ላይ የነበረ በማስመሰል በሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ በመፈረሙ በፈጸመው የሥራ ኃላፊነትን ባለመወጣት የሙስና ወንጀል ተከስሷል። በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በግብረአበርነት በፈጸሙት የሙስና ወንጀል ግምቱ 1ነጥብ7ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መድኃኒት ኬሚካሎች ሰፕላይስ እና የሕክምና መሣሪያዎችን በመዝረፋቸው ኮሚሽኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ች

በሲዳማ ዞን ይርጋአለም ከተማ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከስድስት መቶ ሺህ ብር በሚበልጥ ገንዘብ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል ገቡ፡

በሲዳማ ዞን ይርጋአለም ከተማ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከስድስት መቶ ሺህ ብር በሚበልጥ ገንዘብ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል ገቡ፡፡ በከተማው በፎቶና ቪዲዮ ስራ የሚተዳደሩት አቶ ናአሚን ፍረሕይወት በበኩላቸው የ5 ሺህ ብር ቦንድ ገዝተው በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ከፍለው ለማጠናቀቅ ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላም በኩል በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ስራ የተሰማሩት ወ/ሮ አበባየሁ ለገሰ የ3 ሺህ ብር ቦንድ የገዙ ሲሆን አምስት መቶ ብር ስጦታ መለገሳቸውንም ገልፀዋል፡፡ የከተማው ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ቦልካ ጉዳዩን አስመልክተው እንደገለፁት የግድቡን ስራ ከዳር ለማድረስ የከተማው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት በተለያዩ ጊዜያት ሰፊ የገንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ በየጊዜው በተደረገው ውይይት በከተማው የሚኖሩ ነጋዴዎች፣ የሐይማኖት ተቋማትና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ቦንድ ለመግዛት ቃል መግባታቸውን የገለፁት ከንቲባው በቃላቸው መሰረት ግዥውን በመፈፀም ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ሪፖርተራችን መለሰ ሱኩሌ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ እንደዘገበው፡፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ መግዛታቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ መግዛታቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለገሰ ላሺ እንደገለፁት በቦንድ ግዥው የተሳተፉት በወረዳው 33 የገጠር ቀበሌያትና 4 ከተሞች የሚኖሩ የተለያዩ የእምነት ተቋማት፣ እድሮች እንዲሁም ሞዴል አርሶ አደሮችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ በተለይም የተፈሪ ኬላ ከተማ ነዋሪዎች የ41 ሺህ 45ዐ ብር ቦንድ እጅ በእጅ ክፍያ በመግዛት ቀዳሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የወረዳው ደህኢዴን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አበበ ዘዳግም በበኩላቸው ህብረተሰቡ ከ5ዐ እስከ 1ዐዐዐ ብር ዋጋ ያለውን ቦንድ ግዥ መፈፀሙን ገልፀዋል ሲል የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/05MiyaTextN704.html

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ በህዝብ የሚመራ የጤና ልማት ስራ እያከናወነ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ በህዝብ የሚመራ የጤና ልማት ስራ እያከናወነ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ ለዚሁም ጽህፈት ቤቱ በ16ቱ ጤና ኤክስቴንሽን ፖኬጆች ዙሪያ አዲስ የትግበራ ስልት በመንደፍ ለጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ለባለሙያዎችና ለሱፐርቫይዘሮች ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ በጽህፈት ቤቱ በሽታ መከላከልና ጤና ማጐልበት ዋና ስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ ማቴዎስ ማልጌ በወረዳው የትግበራ ስልቱን ውጤታማ ለማድረግ በሁሉም ቀበሌያት የጤና ልማት ሰራዊት መገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዋናነትም የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ እንደሚሰራ ጠቁመው በዚሁ መሰረት ነፍሰጡር እናቶች በወረዳው በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ በማስጨበጥ ረገድ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል፡፡ የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሸን ጉዳዮች ጽሀፈት ቤት እንደዘገበው፡፡

ባለፉት 7 ወራት ከልዩ ልዩ የገቢ አርእስቶች ከ128 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የሲዳማ ዞን ገቢዎች ባለስልጣን ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ባለፉት 7 ወራት ከልዩ ልዩ የገቢ አርእስቶች ከ128 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የሲዳማ ዞን ገቢዎች ባለስልጣን ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡አፈፃፀሙ ካለፈው ዓመት ብልጫ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ተሻለ ቡላዶ እንዳሉት ከመደበኛ ገቢ 116 ሚሊዮን ከማዘጋጃ ቤቶች ደግሞ 12 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ በታክስ ክፍያ ዙሪያ ያላቸው ግንዛቤ ማደግ ለገቢው መጨመር አስተዋፅኦው የጐላ እንደነበር መግለፃቸውንም የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/25MegTextN404.html

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ግንባታ ከ33 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ እየተሰራ ነው፡

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ግንባታ ከ33 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ እየተሰራ ነው፡፡በወረዳው በመገንባትና በመጠገን ላይ የሚገኙት መንገዶች ሁሉም ቀበሌያት ከወረዳዋ ዋና ከተማ የሚያገናኙ ናቸው፡፡የወረዳው የመንገዶችና ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ድንቅነህ አለማየሁ ግንባታዎቹ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሱታል፡፡ በተለይ ወረዳውን ከኦሮሚያ ክልል የሚያገናኘው ሔማ የተባለው የ18 ኪሎ ሜትር መንገድ ሲጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የላቀ እንደሆነ መግለፃቸውንም የሲዳማ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/25MegTextN504.html

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ፡፡

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀች፡፡ከአሁን በፊት በከተማው የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሲሆን አዲስ አሠራር ችግሩን መቅረፍ እንደሚችል ነው ነዋሪዎቹ የተናገሩት፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ አሠራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡በአገራችን አብዛኞቹ በሽታዎች የሚከሰቱት በግልና በአካባቢ ንጽህና ጉድለት ነው፡፡ችግሩን በቀላሉ መቅረፍ እንዲቻል  በደየደረጃው የጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም ተዘርግቶ የግልና የአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ዙሪያ ትምህርት በመስጠት በንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እየተቻለ ነው፡፡ ቀደም ሲል በሀዋሣ ከተማ የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ቆሻሻው በሚጣልባቸው አካባቢዎች በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይፈጥር እንደነበር ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት፡፡በአሁኑ ሰዓት ከየአቅጣጫው የሚሰበሰበው ደረቅ ቆሻሻ በማጠራቀሚያ ቦታ ላይ ተከማችቶ ሳይቆይ ከአፈር ጋር የማደባለቅ ሥራ በመሠራቱ በአካባቢው የሚፈጠረው መጥፎ ሽታ እየቀነሰ መምጣቱን ነው አንዳንዱቹ የሚያስረዱት፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ብሩ ወልዴ በበኩላቸው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓቱ በህብረተሰቡ ጤናና  አካባቢ ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ጥናት ተደርጐበት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀዋል፡፡ከደረቅ ቆሻሻ ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ኘላስቲኮች በንፋስ እየተነሱ አካባቢን እንዳይበክሉ ለማድረግ ለብቻ ተለቅመው ተመልሰው አገልግሎት ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ ከተለያዩ አካባቢዎች በአህያ ጋሪ የሚጓጓዘው ደረቅ ቆሻሻ በከተማ ውስጥ የሚ

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ ፡፡ የጽህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የተቋማት አስተዳደር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ተወካይ አቶ ባንታየሁ ጉዲሳ አንደገለፁት በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ኘሮግራም እቅድ ከተያዙት 17 ምንጮች የ12ቱ ግንባታ 87 በመቶ ተጠናቋል ፡፡ የግንባታው ወጪም 85 በመቶ ትንሳኤና ብርሃን በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት የሚሸፈን ሲሆን 15 በመቶ በወረዳው በጀት ይሸፈናል ፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ የወረዳው የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 38 ነጥብ 8 በመቶ ይደርሳል ማለታቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ዘግቧል ፡፡

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ በግማሽ የበጀት ዓመት በአፈፃፀማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 6 ቀበሌየት የማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ፡፡

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ በግማሽ የበጀት ዓመት በአፈፃፀማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 6 ቀበሌየት የማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ፡፡የወረዳው ምክር ቤት በ6 ወር የእቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ከቀበሌ አፈ ጉባኤዎች፣ ሊቀነ መናብርትና ሥራ አስኪያጆች ጋር ሰሞኑን ውይይት አካሂዷል፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ በላይነሽ ብዙነህ እንደተናገሩት ቀበሌያቱ ሊሸለሙ የቻሉት ደረጃውን የጠበቀ የቀበሌ ምክር ቤት በማቋቋም የህብረተሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ፈጣን አገልግሎት መስጠት በመቻላቸው ነው፡፡ ቀበሌያቱ ለተለያዩ የልማት ሥራዎት የቅርብ ድጋፍና ክትትል በማድረግ እንዲሁም በየወሩ የሸንጎ አባላት ጉባኤ በማካሄድ ለወረዳ ምክር ቤት ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት በማቅረባቸው ጭምር መሆኑንም አስረድተዋል፡፡የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዘግቧል፡፡

የሀዋሳ ከተማን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ የቱሪዝም ማዕከል ለማደረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ነዋሪዎች ገለጹ

  የሀዋሳ ከተማን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ነዋሪዎች ከከተማው አስተዳደሩ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡ የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የመንግስት ሰራተኞችና የንግዱ ማህበረሰብ ጨምሮ በከተማው ስምንቱም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የጽዳትና የተተከሉ የዛፍ ችግኞችን የመንከባከብ የስራ ዘመቻ ትናንት ተካሄዷል፡፡ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ በየክፍለ ከተማው ተዘዋውረው በስራው የተሳተፉትን ነዋሪዎች አበረታትዋል፡፡ "እያንዳንዱ አካባቢውን ካጸዳ ከተማዋ የጸዳች ትሆናለች" በሚል መርህ ትናንት ለግማሽ ቀን በተካሄደው የስራ ዘመቻ ከተሳተፉት መካከል በባህል አዳራሽ ክፍለ ከተማ የሀረር ቀበሌ ነዋሪው ወጣት ሙሉቀን አለማየሁ በሰጠው አስተያየት አካባቢቸውን ከቆሻሻና ከብክለት ለመከለካል ከሰፈር ጓደኞቹና ነዋሪው ጋር በራሳቸው ተነሳሽነት የጽዳት ዘመቻውን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ብቻ ሳይሆን በቋሚነት በየሳምንቱ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ አካባቢያቸውን ከፍሳሽና ከደረቅ ቆሻሻ ማዕዳት ለጤናቸው ብሎም ለሀዋሳ ውበትና አረንጓዴ ልማት የላቀ አስተዋጾኦ እንዳለው በመገንዘብ በቀጣይም ከከተማው አስተዳደርና ማዘጋጃ ቤት ጋር በመተባበር የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የዚሁ ክፍለ ከተማና ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አሰለፈች በቀለ በበኩላቸው ሀዋሳ ያላትን ጽዳትና ውበት ለማስጠበቅ ጽዳትን ከቤታቸውና ከመንደራቸው በመጀመር እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የመሃል ክፍለ ከተማ ቀበሌ 02 ነዋሪ ወይዘሮ እናኑ መዘምር በሰጡት አስተያየት ጽዳት ለጤንነትና ለከተማ ውበት ወሣኝ መሆኑን በመረዳት ቆሻሻን ከአካባ

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ፡፡

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀች፡፡ከአሁን በፊት በከተማው የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሲሆን አዲስ አሠራር ችግሩን መቅረፍ እንደሚችል ነው ነዋሪዎቹ የተናገሩት፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ አሠራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡በአገራችን አብዛኞቹ በሽታዎች የሚከሰቱት በግልና በአካባቢ ንጽህና ጉድለት ነው፡፡ችግሩን በቀላሉ መቅረፍ እንዲቻል  በደየደረጃው የጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም ተዘርግቶ የግልና የአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ዙሪያ ትምህርት በመስጠት በንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እየተቻለ ነው፡፡ ቀደም ሲል በሀዋሣ ከተማ የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ቆሻሻው በሚጣልባቸው አካባቢዎች በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይፈጥር እንደነበር ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት፡፡በአሁኑ ሰዓት ከየአቅጣጫው የሚሰበሰበው ደረቅ ቆሻሻ በማጠራቀሚያ ቦታ ላይ ተከማችቶ ሳይቆይ ከአፈር ጋር የማደባለቅ ሥራ በመሠራቱ በአካባቢው የሚፈጠረው መጥፎ ሽታ እየቀነሰ መምጣቱን ነው አንዳንዱቹ የሚያስረዱት፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ብሩ ወልዴ በበኩላቸው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓቱ በህብረተሰቡ ጤናና  አካባቢ ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ጥናት ተደርጐበት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀዋል፡፡ከደረቅ ቆሻሻ ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ኘላስቲኮች በንፋስ እየተነሱ አካባቢን እንዳይበክሉ ለማድረግ ለብቻ ተለቅመው ተመልሰው አገልግሎት ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ ከተለያዩ አካባቢዎች በአህያ ጋሪ የሚጓጓዘው ደረቅ ቆሻሻ በከተማ ውስጥ የሚ

በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው በተለምዶ አሞራ ገደል የሚገኘው የፍቅር ሀይቅ በቆሻሻ እየተበከለ ነው

Image
በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው በተለምዶ አሞራ ገደል የሚገኘው የፍቅር ሀይቅ በቆሻሻ እየተበላሸ ሲሆን ሀይቁ በፌስታል፤ በጫት ገራባ፤ በብሰኩትና የመስቲካ ማሸጊዎች እየተጣለ ተቖጣጣሪ ባለቤት ያጣ ይመስላል፡፡ዛሬ እሁድ አፕሪል 15/2012 አካባቢውን የጎበኘሁ ሲሆን የመግቢያ ገንዘብ የሚስከፍሉ Sidama Development Association Hawassa Serial No.272892 ካርኒ ለሁለት ሰው 10 ብር የከፈልኩ ሲሆን ለምን በየተራ የተመደቡ ሰዎች ለምን እየተከታተሉ እነደማያፀዱ ጥይቄያቸው እናፀዳዋለን ከማለት በስተቀር የአንድ ቀን ቆሻሻ ስለማይመስል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡እጅግ አሳዛኙ ነገር የከተማው ድሬኔጅ ኔትወርክ ከሐይቁ ጋር ሜያዙ እጅግ አሳፋሪ ስራ አየተሰራ መሆኑን የከተማው አካባቢ ተቆርቋሪዎች እየሞገቱ ሲሆን እስከአሁን ሰሚ ጆሮ ባለመገኘቱ የአካባቢ ተቆርቋሪዎች ድምፃቸውን ሳይሰለቹ በማሰማት ይህችን ውብ ከተማ ከብክለት ሊታደጓት ይገባል እያሉ ነው፡፡ በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት ቖሻሻ በአሞራ ገደል የፍቅር ሀይቅ በዚሁ ዕለት የተነሳ ነው፡፡  by Melaku Ayele from Hawassa

ለሁለት ቀናት በሀዋሣ ሲካሄድ የቆየው የሲዳማ ዞን ምክር ቤት 3ኛ ዙር 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሦስት የዞን ካቢኔዎችን ሹመትና ከ32 ነጥብ 8 በላይ ተጨማሪ በጀት በማፅደቅ ተጠናቀቀ፡፡

ለሁለት ቀናት በሀዋሣ ሲካሄድ የቆየው የሲዳማ ዞን ምክር ቤት 3ኛ ዙር 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሦስት የዞን ካቢኔዎችን ሹመትና ከ32 ነጥብ 8 በላይ ተጨማሪ በጀት በማፅደቅ ተጠናቀቀ፡፡የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማሊዮን ማቴዎስ ለም/ቤቱ በእጩነት ያቀረቧቸው ካቢኔዎች የዞኑ ግብይትና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ የከተማ ልማት መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ በመሆን በም/ቤቱ ሙሉ ድምፅ መመረጣቸው ታውቋል፡፡ በተጨማሪም ም/ቤቱ ለቀጣይ ወራት የዞን ማዕከል፣ 19 ወረዳዎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲሁም ለሰራተኞች ደመወዝ ክፍያ የሚጠቀሙበትን ከ32 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ በጀት ማፅደቁ ተመልክቷል፡፡ በም/ቤቱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሲምቦ ሽብሩ የተጨማሪ በጀት ደንብ ሰነድ ለም/ቤቱ አባላት ሲያቀርቡ ከተመደበው ተጨማሪ በጀት ከ6 ነጥብ 9 በላይ ሚሊዮን በ2ዐዐ3 የበጀት አመት በተለያዩ ምክንያት ስራ ላይ ያልዋለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ቀሪው ከ25 ነጥብ 9 በ ላይ ሚሊዮን በጀት ደግሞ የዞኑ ማዕከል፣ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ከእቅዳቸው በላይ የሰበሰቡት መሆኑን አቶ ሱምቦ መጠቆማቸውን የዘገበው የዞኑ ባህል ቱሪዝም የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው፡፡

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡ የጽህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የተቋማት አስተዳደር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ተወካይ አቶ ባንታየሁ ጉዲሳ አንደገለፁት በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ኘሮግራም እቅድ ከተያዙት 17 ምንጮች የ12ቱ ግንባታ 87 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የግንባታው ወጪም 85 በመቶ ትንሳኤና ብርሃን በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት የሚሸፈን ሲሆን 15 በመቶ በወረዳው በጀት ይሸፈናል፡፡ግንባታው ሲጠናቀቅ የወረዳው የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 38 ነጥብ 8 በመቶ ይደርሳል ማለታቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ዘግቧል፡፡ Source: http://www.smm.gov.et/_Text/20MegTextN404.html