Posts

Showing posts from March, 2012

የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

Image
የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታደሰ አነቦ ባለፉት ወራት የእናቶችን ሞት ለመቀነስ በተደረገው እንቅስቃሴ ለ2 ሺህ 985 እናቶች የቅድመ ወሊድና የድህረ ወሊድ ምርመራ እንዳደረገላቸውም ተናግረዋል፡፡ 14 ሺህ 49ዐ እናቶች የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተው ቁጥራቸው በተጨማሪም እናቶች በባለሙያ የተደገፈ የወሊድ አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡በአንፃሩ የህፃናትን ሞት ለመቀነስ በተደረገው ርብርብ 3 ሺህ 383 ህፃናት የተለያዩ በሽታዎችን የሚከላከል ክትባት ማግኘታቸው መለሰ ሱኩሌ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል፡፡ ምንጭ:  http://www.smm.gov.et/_Text/16MegTextN304.html

ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በሚበልጥ ወጪ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታው ስራ እየተከናወነ መሆኑን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በሚበልጥ ወጪ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታው ስራ እየተከናወነ መሆኑን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የተቋማት አስተዳደር ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ዘለቀ በላይነህ እንደገለፁት ህብረተሰቡን ከውሃ ወሊድ በሽታ ለመታደግና የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ የዘጠኝ አነስተኛና መለስተኛ የውሃ ተቋማት ግንባታዎች እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ እየተገነቡ ከሚገኙ መካከልም 1 የጥልቅና 3 መለስተኛ የውሃ ጉድጓድ እንዲሁም 5 የአዳዲስ ምንጮች ግንባታ እንደሚገኝ አስተባባሪው አስረድተዋል፡፡ሲል መለሰ ሱኩሌ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል፡፡

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በመጠጥ ውኃ እጥረት መቸገራቸውን የመጆ ከተማ ነዋሪዎች አስታወቁ፡፡

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በመጠጥ ውኃ እጥረት መቸገራቸውን የመጆ ከተማ ነዋሪዎች አስታወቁ፡፡በተከሰተው የውሀ እጥረት የተነሳ ለህብረተሰቡ የተሟላ የጤና አገልግሎት ለመስጠት መቸገሩን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አመልክቷል፡፡ የወረዳው ውኃ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት በበኩሉ ችግሩ እስከ ሚያዚያ 3ዐ ባለው ጊዜ ይፈታል ብሏል፡፡የመጆ ከተማ የአሮሬሳ ወረዳ ዋና ከተማ ስትሆን ዙሪያዋ 8 በሚበልጡ የተፈጥሮ ምንጮች የተከበበች ናት፡፡ ይሁንና ምንጮቹ በበጋ ወራት መድረቅ በመጀመራቸው በተለይም ካለፈው አመት ጀምሮ ለከፍተኛ የመጠጥ ውኃ ችግር መጋለጣቸውን ነው ነዋሪዎች የተናገሩት፡፡አንዳንዶቹ እንደሚሉት በውኃ ማድያ ወረፋ ለመያዝ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ጀምሮ ከቤት ስለሚወጡ ዘረፋና ድብደባ እንደሚደርስባቸውና ለተለያዩ በሽታዎች እንደሚጋለጡ ተናግረዋል፡፡ የወረፋውን ሰልፍ ይዘው እስከ እኩለ ቀን ድረስ እንደሚቆዩ የገለፁት ነዋሪዎቹ በዚህም የተነሳ በረሃብ እንደሚጐዱና ወረፋው ሳይደርሳቸው ሲቀር ደግሞ በዐ.5ዐ ሣንቲም የሚገዛውን ባለ 2ዐ ሊትር አንድ ጀሪካን ውኃ ከአትራፊዎች ከ5 እስከ 6 ብር ለመግዛት እንደገደዳለን ብለዋል፡፡ እነዚህ አትራፊዎች ከከተማው በቅርብ ርቀት ላይ ከሚገኘውና ጪጩ ከተባለ ወንዝ ንጽህናው ያልተጠበቀ ውኃ ቀድተው ስለሚሸጡላቸው ለተለያዩ ውኃ ወለድ በሽታዎች እየተጋለጡ እንደሚገኙ አስድተዋል፡፡የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት በበኩሉ በከተማው በተፈጠረው የውኃ ችግር የተነሳ ለህብረተሰቡ ንፅህናውን የተጠበቀ የጤና አገልግሎት መስጠት አለመቻሉን አመልከቷል፡፡ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙንጣሽ ብርሃኑ እንዳሉት በከተማውና በአካባቢው የሚገኙ 4 ጤና ጣቢያዎች ከመኝታና ከመፀዳጃ አገልግሎቶች አንስቶ ለህሙማኑ ደረጃውን የጠበቀ የጤና አ

የዳዬ በንሳን ጨምሮ በደቡብ ክልል ከ263 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ ስድስት የቴክኒክ ሙያና ትምህርት ስልጠና ኮሌጆች ስራ ጀመሩ

አዋሳ, መጋቢት 20 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክልል ከ263 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተጀመሩ ስድስት የቴክኒክ ሙያና ትምህርት ስልጠና ኮሌጆች ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የክልሉ ቴክኒክ መያና ትምህርት ስልጠና ቢሮ ገለጸ፡፡ የኮሌጆቹ መገንባት በክልሉ ያሉት መሰል ኮሌጆች ብዛት ወደ 22 ያሳድገዋል ። በቢሮው የልማት ዕቅድ ፣ ዝግጅት፣ ክትትልና ግብረ መልስ የስራ ሂደት ባለቤት አቶ ኢዮብ አዳ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በ2002 ግንባታቸው ተጀምሮ ዘንድሮ የተጠናቀቁት ኮሌጆች በሳውላ ፣ በተርጫ ፣በጂንካ በሃላባ ፣ በወራቤና በዳዬ ከተሞች የሚገኙ ናቸው፡፡ ለኮሌጆቹ የመምህራን ቅጥር በማከናወንና የውስጥ ድርጅት በማሟላት በአሁኑ ወቅት ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብለው በአጫጭር ፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ የስልጠና ፕሮግራም መጀመራቸውን አመልከተዋል፡፡ ኮሌጁቹ ከሚያሰለጥኑባቸዉ መስኮች መካከል ኮንስትራክሽን ፣ አውቶሞቲቨ ፣ ብረታብረት ፣ ኤሌክትሪክ ሲቲ ፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ጨርቃጨርቅና ቆዳ ቴክኖሎጂ እንደሚገኙባቸዉ የስራ ሂደቱ ባለቤት አስረድተዋል፡፡ ተቋማቱ በውስጣችው ቤተ መጻህፍት ፣ ቤተ ሙከራ ፣ የመማሪያ ክፍሎች ፣ ቢሮዎችና ሌሎችም ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚያገለግሉ ከ12 እስከ 13 ክፍሎች ማካተታቸወን ጠቁመው የግንባታቸው ወጪ ሙሉ በሙሉ በመንግስት የተሸፈነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተቋማቱ መገንባት የህብረተሰቡንና የገበያው ፍላጎት መሰረት በማድረግ ውጤታማና የተቀናጀ ስልጠና በመስጠት ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ስራላይ የሚሰማሩ ባለሙያዎች በብዛትና በጥራት በማፍራት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድን ለማሳካት በተለይ ወደ ኢንዱስትሪው መር ልማት ለመሸጋገር ከፍተኛ

Aid Approved for Kenya Highway, Geothermal Projects - AfDB is funding improvements to a 198-km road section in Ethiopia, from Hawassa to Ageremariam, which will connect with the Turbi-Moyale segment

Image
The government of Kenya and the African Development Bank have signed agreements totaling $366 million in financial aid for two projects: a geothermal steam field and a road upgrade, which will open landlocked Ethiopia to the Indian Ocean port of Mombasa.  Kenya’s finance minister, Njeru Githae, and the African Development Bank (AfDB) regional director for East Africa, Gabriel Negatu, signed the agreements on March 12. Of the total assistance, a $186.7-million loan from the AfDB group’s African Development Fund will go for converting what is now a 122-kilometer gravel road to an asphalt-paved highway. The upgraded road segment, from Turbi to Moyale, will include bridges and a drainage system. It will have two lanes up to seven meters wide in each direction as well as shoulders. Separately, AfDB is funding improvements to a 198-km road section in Ethiopia, from Hawassa to Ageremariam, which will connect with the Turbi-Moyale segment.  Kenya and Ethiopia hav

A stroll through Awasa

Image
A stroll through Awasa February 9, 2012 arefe Leave a comment Go to comments Walking along the asphalted streets of Awasa, among the crowds of high school and university students, merchants, aid workers, and cycle commuter, it’s hard to imagine that not so long ago these streets were dirt tracks. Awasa was founded only fifty years ago. As the capital of the southern region, it rapidly became a boom town. Benefiting from the de-centralization policy of the government, a construction rush over the past decade has transformed the town, ushering in a new mood of optimism and enterprise. The new structures, interspersed with palm trees and newly opened restaurants, are making the town increasingly vibrant.The lakeside locations have especially made Awasa a favored destination for weekenders from Addis Ababa and the recently opened Lewi and Haile Resort are particularly popular. With over 126,000 residents, Awasa is one of the fastest growing Ethiopian towns. Smallest of the

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ አስተዳደር ባለፈው ግማሽ የበጀት ዓመት በህብረተሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና በመልካም አስተዳደር ተቃሚነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራት ማከናወኑን አስታወቀ፡

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ አስተዳደር ባለፈው ግማሽ የበጀት ዓመት በህብረተሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና በመልካም አስተዳደር ተቃሚነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባራት ማከናወኑን አስታወቀ፡፡የአስተዳደሩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን መንግስቱ እንደገፁት በተጠናቀቀው ግማሽ የበጀት ዓመት 13ዐ የህዝብ አቤቱታዎች ለወረዳው አስተዳደር ቀርበው እልባት ላይ እንዲደርሱ ተደርጓል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶችና ጊዜያት የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ሰው ሠራሽ እግርና ባለ ብረት የአካል ድጋፍ ተገዝቶ አንደተሰጣቸው ጠቁመዋል፡፡የገንዘብ ችግር ያለባቸው 28 ሰዎች በይርጋለም ሆስፒታልና ጤና ጣቢያ ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን አቶ ተመስገን መግለፃቸውን የዘገበው የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው፡፡ Source: http://www.smm.gov.et/_Text/14MegTextN204.html  

በወንዶ ገነት አካባቢ በሚገኘው በተፈጥሮ ደን ላይ ተነስቶ የነበረው የሰደድ እሳት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ፡፡

Image
በወንዶ ገነት አካባቢ በሚገኘው በተፈጥሮ ደን ላይ ተነስቶ የነበረው የሰደድ እሳት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ፡፡ በሲዳማ ዞን የወንዶ ገነት ወረዳ የመንግስት ኮሚኒኬሽን  የጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ጉራቻ እንደገለፁት መጋቢት 8 ቀን 2ዐዐ4 ዓ/ም ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ ባልታወቀ ምክንያት ተነስቶ የነበረው ሰደድ እሳት ለ2 ተከታታይ ቀናት በመቆየቱ በ2ዐዐ ሄክታር መሬት ላይ የነበረ የተፈጥሮ ደን ሊወድም ችሏል፡፡ በተነሳው የሰደድ እሳት ምክንያት በርካታ ብርቅዬ አዕዋፋትና የዱር እንስሳት ከቦታው መሰደዳቸውን የገለፁት ምክትል ኃላፊው የእሳቱን መንስኤ ለማጣራት የወንዶ ገነት ደን ኮሌጅ ጉደዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ጥናት እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የእሳቱን ኃይል በቁጥጥር ስር ለማዋል የፌዴራል ፣ የዞንና የወረዳው ፖሊስ እንዲሁም የኮሌጁ ሠራተኞችና የአካባቢው ህብረተሰብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረሃጋቸውንም ገልፀዋል፡፡ የወንዶ ገነት ደን  ኮሌጅ ማነጂንግ ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ አክሊሉ በአካባቢው በየዓመቱ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ በደኑ ላይ የሰደድ እሳት የሚለቁ ግለሰቦች እንደሚስተዋሉ አውስተው ይህ ተግባር ህዝብንና መንግስትን የሚጐዳ በመሆኑ ከድርጊታቸው ሊቆጠቡና ደኑን በባለቤትነት ሊጠብቁ እንደሚገባቸው ገልፀዋል ሲል ሪፖርተራችን ካጀ ጀንቦላ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያችን ዘግቧል፡፡ Source:  http://www.smm.gov.et/_Text/14MegTextN404.html

New State of the Art Southern Nationalities, Nations and Peoples Region Regional Laboratory in Hawassa City

Image
New State of the Art Southern Nationalities, Nations and Peoples Region Regional Laboratory in Hawassa City Fig 1: His Excellency President Shiferaw Shegute Right top corner: Rendering of the SNNPR Regional laboratory SNNPR President H.E Shiferaw Shegute, Ethiopian Minister of Health, Dr. Tedros Adhanom, Ato Kare Chawicha Regional Health Bureau Head and Country Director of the United States’ Center for Disease Control and Prevention (CDC) Dr. Tom Kenyon, and invited guests broke ground on the construction of a new SNNPR Regional Laboratory in the city of Hawassa in SNNPR on June 30, 2011 within walking distance from the Hawassa Regional Referral Hospital The New SNNPR Regional Laboratory will augment the current Hawassa Regional Laboratory, which is one of the six regional labs in the country to be upgraded to support DNA PCR and TB culture, DST and Molecular Diagnostic Laboratory supporting four sub-regional laboratories situated in Hossana, Arbaminch, Mizan and Jinka. The Ne

በደቡብ ክልል አዲሱ የሊዝ አዋጅ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል -የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር

Image
በደቡብ ክልል አዲሱ የሊዝ አዋጅ ከዛሬ ጀምሮ በየደረጃው ተግባራዊ እንደሚሆን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የንግድ ፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ሀላፊ አስታወቁ ። በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ህብረተሰቡም ለአዋጁ ተግባራዊነት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የቢሮው ሃላፊ አቶ ታገሰ ጫፎ ትናንት ለጋዜጠኞች እንደገለጹት በሀገር ደረጃ ህዳር 18/2004 የጸደቀው አዲሱ የሊዝ አዋጅ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ መሬት የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዘቦች የጋራ ሀብት እንደመሆኑ የከተማ ቦታ በሊዝ ጨረታ ወስዶ ያለማ ሰው እሴት እንደሚፈጥርለትና ተጠቃሚ እንደሚሆን አስታዉቀዋል ። በአዋጁ መሰረት የተከለከለው ባዶ መሬት በሊዝ ከወሰደ በኋላ ሳይሰራበት መሬቱን አሲዞ አለአግባብ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር ከባንክ መበደርና መሸጥ ነው ብለዋል፡፡ መሬት ልማታዊ ባልሆነ መንገድ ወስዶ በአቋራጭ መበልጸግና ሀብት ማግበስበስ እንደማይቻል በአዋጁ ላይ በግልጽ መደንገጉን ያስረዱት አቶ ታገሰ በዚህ ዐይነት ህገ ወጥ አካሄድ የመሬት ዋጋ ጣሪያ ከመድረሱም በላይ ለልማት የሚውለው ገንዘብ በመሬት ግዥና ሽያጭ እየባከነ ችግር መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ የመሬት አስተዳደር ስርዓትና የመሬት አቅርቦትን ከከራይ ሰብሳቢነት የጸዳ ለማድረግ አዋጁ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አመልከተው በፕላን መሰረት ቤት የሰራና በዙሪያው ያለማውን ሀብት መሸጥ እንደሚችል ፣ ነገር ግን መሰረት በመጣልና ከ50 በመቶ በታች ግንባታ በማካሄድ በከፍተኛ ገንዘብ መሸጥ የማይቻል መሆኑን ህዝቡ በግልጽ መገንዘብ እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ነባር ይዞታዎች በውርስ ማስተላላፍ እንጂ ወደ ሊዝ የሚገባን መሬት ለሶስተኛ ወገን

Ethiopian Coffee Exports Decline

The export of coffee from  Ethiopia  has declined by 38% in the first eight months of the financial year, as compared to the same period last, according to data from players in the sector. The Ethiopia Commodity Exchange has consequently eliminated the 5% +/- price range for coffee intended to regulate against price fluctuations on the international market last week. The range will not be applicable on the trading floor of  Exchange until the price of coffee stabilizes on the international market said Dr. Eleni Z. Gebremedhin, Chief Executive of the ECX. It is estimated that the annual coffee production of Ethiopia for this harvest year will be 8,312,000 bags or 498,720 tons according to forecasts made by the International Coffee Organization.  Ethiopia expects to export 50% of its coffee production amounting to an estimated 249.5 tons this year. Coffee exports in the first eight months of the fiscal year, however have only added up to 75,000 tons. The decrease in  coffee sh

የቡና ዋጋ ወሰን ሙሉ ለሙሉ ተነሳ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የቡና መገበያያ  የዋጋ ወሰንን ከትናንት በስቲያ ገበያ መዝጊያ ዋጋ አኳያ ወደ ላይና ወደ ታች የአምስት በመቶ ጭማሪና ቅናሽ እንዲያሳይ በማድረግ ሲያገበያይበት የነበረውን አሠራር ላልተወሰነ ጊዜ ማንሳቱን አስታወቀ፡፡ የምርት ገበያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድኅን ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ የዋጋውን ወሰን ማንሳት ያስፈለገው በኒውዮርክ ዓለም አቀፍ ገበያ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የቡና ዋጋ፣ ባለፈው ሐሙስ ዕለት በፓውንድ (ግማሽ ኪሎ ገደማ) አንድ ዶላር ከሰባ አምስት ሳንቲም የሆነ ዝቅተኛ ዋጋ በማስመዝገቡ የዋጋ ወሰኑን ሙሉ ለሙሉ ማንሳት አስፈልጓል፡፡ የዓለም የቡና ዋጋ እስኪስተካከል ድረስ የዋጋ ወሰኑ ሙሉ ለሙሉ ተነስቶ እንደሚቆይ የገለጹት ዶክተር እሌኒ፣ የአገር ውስጥ አቅራቢዎች የቡና ዋጋ መው ረዱን የማይቀበሉት ከዚህ ቀደም የተሻለ ዋጋ ለማግኘት አስበው በእጃቸው ያቆዩት ቡና ይበልጥ ዋጋው ሲወርድ ለኪሳራ ስለሚያጋልጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ይህም ሆኖ አቅራቢዎች በግድ ሽጡ እንዳልተባሉ ገልጸው፣ ምርቱን በእጃቸው ከማቆየት ይልቅ ግን እንዲህ ያለ ያልታሰበ የዋጋ ማሽቆልቆል እንዳይከሰት በእጃቸው ያለውን ቡና ቶሎ ለገበያ እንዲያቀርቡ መክረዋል፡፡ ከሦስት ወራት በፊት የቡና ዋጋ እስኪጨምር ድረስ ምርቱን በእጃቸው ይዘው ሲጠባበቁ የነበሩ አቅራቢዎች የዋጋው መውረድ እንደጎዳቸው ገልጸው፣ አምና በፓውንድ ሦስት ዶላር ያወጣ የነበረው ቡና ባለፈው ወር ወደ ሁለት ዶላር ሊወርድ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ በዚህ ያላቆመው የዋጋ ማሽቆልቆል ከሁለት ሳምንት በፊት የኒውዮርክ ገበያ ዋጋው ወደ አንድ ዶላር ከዘጠና ሊወርድ መቻሉን፣ ባለፈው ሐሙስ ደግሞ ብሶበት አንድ ዶላር ከሰባ አምስት ሳንቲም ማውጣቱን ይገልጻሉ፡፡  በአንፃሩ በምርት

በሐዋሳ በተነሳው የእሳት አደጋ ንብረት አወደመ: በሐዋሳ ከተማ የንግድ ተቋማት ባለንብረቶች: ከኢንሹራንስ ይልቅ ማኅበራዊ ተራድኦን የሚመርጡ መሆናቸው ተነገረ

Image
 በአደጋው የከተማው አስተዳደር እሳት አደጋ መከላከል አቅም ተፈትሿል መጋቢት 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ በሐዋሳ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በሁለት መደብሮች የተነሳው እሳት ንብረት አወደመ:: ወደ ክብሩ ሆስፒታል መሄጃ ላይ እየሩሳሌም የጨርቃ ጨርቅ መደብርንና አጠገቡ ያለው ጥሩወርቅ የኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት በእሳቱ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን፣ ባለንብረቶቹ እንደሚሉት 1.3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በተነሳው እሳት የእሳት አደጋ መከላከያ በወቅቱ ባለመድረሱና ዘግይቶ ከደረሰም በኋላ አቅሙ ውስን በመሆኑ፣ በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት ማዳን እንዳልተቻለ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ እንደ እማኞቹ አስተያየት ያለምንም መከላከያ ለ20 ደቂቃዎች ያህል ሲቀጣጠል የነበረው እሳት፣ በመደብሮች ውስጥ የነበሩትን ጨርቃ ጨርቆችና ኮምፒውተሮች በፍጥነት ጋይተዋል፡፡ የእየሩሳሌም ጨርቃ ጨርቅ መደብር ባለቤት አቶ ጌቱ ደምቦባ ስለደረሰው ጉዳት ተጠይቀው፣ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጣቃዎችና የተዘጋጁ ልብሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸው፣ የእሳቱን መንስዔ በተመለከተ ለተጠየቁት ሲመልሱ፣ ማናቸውንም የኤሌክትሪክ ዕቃዎችንና ካውያዎችን በአግባቡ ካጠፉ በኋላ መደብራቸውን መዝጋታቸውንና እሳቱ ከየት እንደተነሳ እንደማያውቁ ለሪፖርተር ጠቁመዋል፡፡ የጥሩወርቅ ኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት ባለቤት በበኩላቸው፣ ከ300 ሺሕ ብር በላይ የሚገመቱ ኮምፒውተሮችና የፎቶ ኮፒ ማሽኖች እንዲሁም የስቴሽነሪ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸዋል፡፡ በምሽቱ የተፈጠረውን እሳት ለመከላከል የሐዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የእሳት አደጋ መከላከያና የከተማው የእሳት አደጋ መከላከያ በአጠቃላይ ሦስት ተሽከ

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡፡

ሀዋሳ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣውን የወላጅ አጥ ህፃናት ቁጥር ችግር ለመፍታታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡

Image
ሀዋሳ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣውን የወላጅ አጥ ህፃናት ቁጥር ችግር ለመፍታታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡መምሪያው ከተለያዩ የዕምነት ተቋማትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሀገሪቱ አዲስ የሆነውን የፎስተር ኬር ኘሮግራም እንደሚጀምርም ገልጿል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ በሀገሪቷ በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ የተጀመረውን የፎስተር ኬር ኘሮግራም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ከቢታኒ ቤተክርስትያን ሰርቪስና ከርሆቦት ዴቨሎኘመንት ኤንድ ሳፓርቲንግ ኦርጋናይዜሽን ጋር በመተባበር ለወንጌላዊያን አብያተክርስትያናት መሪዎች መምሪያው ባዘጋጀው የምክክር ስብሰባ ላይ እንደተባለውም በከተማው የፎስተር ኘሮግራም ለመጀመር ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሪት ስምረት ግርማ እንዳሉት ከ4 ወራት በኋላ የሚጀመረው የፎስተር እንክብካቤ በከተማው በህፃናት ማሳደጊያ ተቋማት የሚገኙ ከ2ዐዐ በላይ ህፃናትን ጨምሮ በየደረጃው በጐዳና ላይ ያሉት ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ ህፃናት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡በኘሮግራሙ ወላጅ አጥ ህፃናትና ተጋላጭ የሆኑ ቤተሰቦች ድጋፍ ያገኛሉ ያሉት ወይዘሪት ስምረት ወላጅ አጥ ህፃናት የቤተሰብ ፍቅር አግኝተው እንዲያድጉ ከቤተሰቦቻቸው ካልሆነም ፈቃደኛ ከሆኑ ሌሎች ቤተሰቦች እንዲያድጉ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡ ኘሮግራሙ የህፃናትን ችግር ለመፍታት ከሚደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንዱ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ህፃናቱን የሚያሳድጉ ቤተሰቦች በየእምነት ተቋሙ የሚመለመሉ በመሆናቸው የእምነት ተቋማት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የህዝቡ የመተሳሰብና የመተባበር ባህል በማጐልበትና በማሳመን ሞራላዊና መንፈሳዊ ግዴታቸው እንዲወጡም

በሲዳማ ዞን በሁሉም ቀበሌያት 2ዐ5 ሺህ 9 መቶ 24 ሄክታር መሬት በተፋሰስ ለማልማት ከታቀደው 75 በመቶ ማከናወን መቻሉን የዞኑ ግብርና ልማት መምሪያ ገለፀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡

US Agency for International Development - Reading for Ethiopia's Achievement Developed (READ) including Sidama Language-- Deadline Extended

US Agency for International Development - Reading for Ethiopia's Achievement Developed (READ) -- Deadline Extended Synopsis: The purpose of this Program Description is to obtain technical assistance and services proposals from qualified institutions for implementation of “Reading for Ethiopia‘s Achievement Developed (READ) Technical Assistance project" in Ethiopia. Recipients should develop technical and financial descriptions for a five-year project that begins on or about May 2012 and ends no later than June 2017. This project will provide an innovative approach to supporting the Ethiopian Ministry of Education‘s (MOE‘s) efforts in developing a nationwide reading and writing program that will reach the vast majority of Ethiopian primary students. This project has a heavy focus on providing technical expertise in international best practices of teaching reading and writing; expertise that is to be applied to a variety of Ethiopian languages in order to develop syllabi, cur

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የተፋሰስ ልማትን ለማጠናከር በውሃ ሀብት ላይ ያተኮሩ ሶስት የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ ነዉ

Image
አዋሳ, መጋቢት 14 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ የተጀመረውን የተፋሰስ ልማት ለማጠናከር በውሃ ሀብት ላይ ያተኮሩ ሶስት የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ ። አለም አቀፍ የውሃ ቀን " ውሀና ምግብ ዋስትና ለሁሉም " በሚል መሪ ቃል ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት በዩኒቨርስቲው ዋናው ግቢ በፓናል ውይይትና በፎቶ ግራፍ አውደ ርእይ ተከብሯል፡፡ የዩኒቨርስቲው ምሁራን በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳስረዱት በሀገራችን የተጀመረው የተፋሰስ ልማት ውሃን በአግባቡ ለመጠበቅና ለመጠቀም በተለይም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለዉ አስተዋጾኦ ከፍተኛ ነዉ ። በዩኒቨርስቲው የመስኖና ውሃ ሀብት ምህንድስና ትምህርት ክፍል ሃላፊ አቶ ሄኖክ ጥላሁን እንደገለጹት የተጀመሩትን አበረታች የተፋሰስ ልማት ስራዎች ይበልጥ ለማጠናከር የርምር ፕሮጀክቶቹ እየተካሄዱ ያሉት በደቡብ ክልል በሀዋሳ ሀይቅ ፣ በብላቴ ወንዝና ሌሎች የተፋሰስ አካባቢዎች ላይ ነዉ ። ከምርምሮቹም መካከል በሀዋሳ ሀይቅ ላይ ከከተማው የተለያዩ አቅጣጫዎች ከሚለቀቁ ዝቃጭ ቆሻሻዎች ለመታደግና የሃይቁን ደህንነቱ ለመጠበቅ ብሎም ለልማት እንዲውል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰሩና የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በደቡብ ክልል ከሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሚያካሄዳቸው የምርምር ስራዎች ወደሌሎችም የሀገራችን አካባቢዎች በማስፋፋት የድርሻውን እንደሚወጣ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው የባዮ ሲስተምና ኢንቫይሮሜንታል ምህንድስና ዲፓርተመንት መምህር አቶ አሰግድ ቸርነት በበኩላቸው በተለይ ተማሪዎችንና ወጣቶች የውሃን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በውል ተገንዝበው እን

Lasting Solutions to Water Challenges | TechnoServe - Business Solutions to Poverty

Lasting Solutions to Water Challenges | TechnoServe - Business Solutions to Poverty ...In the Sidama region of Ethiopia,  coffee  is a vital source of income. But coffee processing can place enormous strain on the region’s limited water resources. In partnership with Mother Parkers Tea & Coffee, TechnoServe is helping 17 coffee wet mills to plant vetiver grass wetlands that will naturally treat and filter waste water from coffee processing. This program will help improve water quality for communities and demonstrate a sustainable model for other wet mills in the region.  ...

Lasting Solutions to Water Challenges | TechnoServe - Business Solutions to Poverty

Lasting Solutions to Water Challenges | TechnoServe - Business Solutions to Poverty New

በሲዳማ ዞን የመጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ እየተካሄደ ነው

Image
አዋሳ, መጋቢት 12 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን ከ97 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት በ19 ወረዳዎች የውሃ ተቋማት ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የዞኑ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለጸ። የመምሪያው ኃላፊ አቶ አብሩ ደቃሞ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በመንግስት፣ በአለም ባንክ፣መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በህብረተሰቡ ተሳትፎ በ19 ወረዳ በመገንባት ላይ ካሉት የውሃ ተቋማት መካከል ጥልቅ ፣መለስተኛና አነስተኛ ጉድጓድ ምንጭ የማጎልበት ይገኝበታል። የአዋዳ ቦርቻ ከፍተኛ ምንጭ ግንባታና ማስፋፊያን በማጠናቀቅ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው ለሸበዲኖና ጎርቼ የሚገነቡ ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች የመገንባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የይርጋለምና አለታ ወንዶ ከተሞች የመጠጥ ውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ለማከናወን ጨረታ ወጥቶ አሸናፊው ግንባታ መጀመሩን ገልጸው ለሁለቱ ከተሞች የመጠጥ ውሃ ግንባታ ከ29 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቀዋል። በዞኑ የተጀመረው የመጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ ከ60 በመቶ በላይ መጠናቀቁን አስታውቀው በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በገንዘብ በቁሳቁስና ጉልበት አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመው ግንባታቸው ሲጠናቀቅ ከ760 ሺህ የሚበለጥ የዞኑ ነዋሪ ተጠቃሚ በማድረግ የዞኑን የውሃ አቅርቦት ሽፋን ከ41 በመቶ ወደ 60 በመቶ እንደሚያሳድገው ገልጸዋል

Cost efficacy of Community-Based and In-Patient Therapeutic Feeding …

This investigate estimated a cost efficacy of community-based healing caring (CTC) for children with serious strident gauntness (SAM) in Sidama Zone, Ethiopia compared to trickery formed healing feeding core (TFC). Methods: A cost efficacy research comparing costs and outcomes of dual diagnosis programmes was conducted. The governmental perspective, that considers costs to all sectors of a society, was employed. Outcomes and health use costs of CTC and TFC were performed from Save a Children USA (SC/USA) CTC and TFC programme, supervision health services and UNICEF( in kind supplies) cost estimates of section costs. Parental costs were estimated by interviewing 306 caretakers. Cost categories were compared and a singular cost efficacy ratio of costs to provide a child with SAM in any module (regardless of outcome) was computed and compared. Results: A sum of 328 studious cards/records of children treated in a programs were reviewed; out of that 306 (157 CTC and 149 TFC) were

"An Assessment of the Impacts of Evangelical Christianity on the socio-cultural and religious transformation of Ethiopian society with specific reference to the southern region especially Sidama"

Seminar: Aklilu Lalegoa Submitted by administrator on Tue, 03/01/2012 - 15:25 Calendar Start:  22/02/2012 11:00 Timezone:  Europe/London "An Assessment of the Impacts of Evangelical Christianity on the socio-cultural and religious transformation of Ethiopian society with specific reference to the southern region especially  Sidama " http://www.ocms.ac.uk/content/index.php?q=node/358  

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/8MegTextN104.html