የሀዋሳን መስህቦች ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ16 ነጥብ 8ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ፡፡


አዋሳ ታህሳስ 3/2005 በሀዋሳ ከተማና አካባቢውን የሚገኙ የመስህብ ቦታዎችን ባለፉት ሶስት ወራት ከጐበኙ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ከ16 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የከተማው አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የቱሪዝምና ፓርኮች የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አዲሴ አኔቶ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ ከተማና አካባቢው የሚገኙ የመስህብ ቦታዎች ባለፉት ሦስት ወራት በ47 ሺህ 728 የሀገር ውስጥና 10 ሺህ 139 የውጪ አገር ቱሪስቶች ተጐብኝተዋል፡፡ ቱሪስቶቹ የጎበኟቸው የመስህብ ቦታዎች የሀዋሳ ሀይቅንና በውስጡ ያሉት ብርቅዬ የአእዋፍ ዝርያዎች፣ ጉማሬዎች ፣ በከተማው ዙሪያ የሚገኙት የአላሙራና የታቦር ተራራዎች፣ የጥቁር ውሃ ደን ፣ የቡርቂቲ ፍል ውሃ ፣ የሲዳማ ባህላዊ ጎጆዎችንና የተለያዩ ብሄረሰቦች የባህል አልባሳት ፣ አመጋገብና የሙዚቃ መሳሪዎች ጨምሮ ሌሎች ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶች ነው፡፡ የተገኘው ገቢም ሆነ የቱሪስቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር አምስት በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ገቢውም ሆነ የቱሪስቶች ቁጥር ሊጨምር የቻለው የቱሪዝም ሀብቱን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በማስተዋወቅ ጎብኚዎችን ለመሳብ በተደረገው ጥረት መሆኑን የስራ ሂደቱ አስተባባሪ አመልከተዋል፡፡ የሀዋሳ ከተማ የአየር ንብረት ተሳማሚነት፣ የመስተንግዶና የመሰረተ ልማት መስፋፋትን ጨምሮ ለመዝናናትና ለኑሮ ባለው ምቹነት አካበቢውን ለመጎብኘት የሚመጡ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ቁጥር በየአመቱ እየጨመረ እንዲሄድ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ የጐብኝዎች ቁጥር መጨመርን ተከትሎም የሚገኘው ገቢ በዚያው መጠን እያደገ መሆኑን አስተባበሪው ጠቁመው የዘርፉን ልማት ይበልጥ ለማጎልበት ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=3912&K=1

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር