አካል ጉዳተኞችን በማቋቋምና በመደገፍ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ማብቃት በሚል የክልሉ አካል ጉዳተኞች ማህበር ያዘጋጀው የኘሮጀክት ትውውቅ መድረክ በአለታ ወንዶ ወረዳ ተካሄደ፡፡

አቶ ባልጉዳ ጳውሎስ የአለታ ወንዶ ወረዳ አካል ጉዳተኞች ማህበር ሊቀመንበር እንዳሉት አካል ጉዳተኞች ካለባቸው ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ተላቀው የበኩላቸውን  አስተዋፅኦ ለማበርከት የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የባለ ድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ተፈራ ጨመሳ የክልሉ አካል ጉዳተኞች ማህበር አማካሪ በበኩላቸው አካል ጉዳተኛችን ለማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ልማት ከማብቃት በተጨማሪ የአካል ጉዳተኛ ህፃናትን የትምህርት ተሳትፎ በማሳደግ የወደፊቱን የትውልድ ተስፋ እንዲያብብ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ለአስሩ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ለእያንዳንዱ ተማሪ በወር 15ዐ ብር ለአስር ወራት ድጋፍ በማድረግ ለሁሉም ተማሪዎች 15 ሺህ ብር ተመድቦላቸው በመማር ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን እንደዘገበው፡፡
http://www.smm.gov.et/_Text/02HidTextN405.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር