ባለፈው ዓመት በሁሉም የልማት እቅዶች አፈፃፀም ላይ የታዩ ክፍተቶችንና ውስንነቶችን ለመቅረፍ መዘጋጀቱን በሲዳማ ዞን የቡርሳ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወረዳው ምክር ቤት 3ኛ ዙር 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ሲካሄድ ዋና አስተደደሪው አቶ አማረ ሻላሞ እንዳሉት  የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት ሁሉም የልማት እቅዶች በጠንካራና በተደራጀ የልማት ሰራዊት መመራት አለባቸው ብለዋል፡፡

በወረዳው በሚከናወነው የበልግና የመኸር እርሻ 7 ሺህ 831 ሄክታር መሬት በዋና ዋና ሰብሎች በመሸፈን 16 ሺህ 584 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀዋል፡፡
ለዚህም15 ሺህ 13ዐ ኩንታል ዳኘና ዩሪያ ማዳበሪያ እንዲሁም አሲዳማ አፈርን በማከም ለእርሻ ሥራ ለማዋል 2ዐዐ ኩንታል ኖራና የተለያዩ ሰብሎች 3 ሺህ 289 ኩንታል ምርጥ ዘር በግብዓትነት እንደሚሠራጭም አቶ አማረ አስረድተዋል፡፡
ጉባኤው ከ39 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በማፅደቅ መጠናቀቁንም የሲዳማ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ዘግቧል፡፡
http://www.smm.gov.et/_Text/02HidTextN505.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር