የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ለመገንባት 63 ሺህ በላይ ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን የሀዋሣ ከተማ ጤና መምሪያ ገለፀ፡፡መምሪያው የ2ዐዐ5ሩብዓመትእቅድክንውንገምግሟል፡፡


የእቅድ ክንውን ሪፖርት በቀረበበት ወቀት የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደሰታ ዶጊሶ አንደተናገሩት በሩብ አመቱ የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የጤናና የማህበራዊ ችግሮች በመፈታት ነዋሪውን ጤናማ፣ አምራችና የበለፀገ ለማድረግ የጤና ልማት ሰራዊት ግንባታ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ከመገንባት አንፃርም ከ63 ሺህ 993 ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን ተናግረዋል፡፡
በሪፖርቱ እንደቀረበው የሳንባ ነቀርሳ በሽታን መከላከያ ክትባት ለ2 ሺህ 678 ህፃናት ለመስጠት ታቅዶ 2 ሺህ 971 የተከናወነ ሲሆን ባለፈው ሩብ አመት አብዛኛዎቹ አፈፃፀሞች ከእቅዱ 9ዐ በመቶ እና ከዚያ በላይ ተግባራዊ መሆናቸው በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡
ከመንጋጋ ቆልፍ በሽታ የተጠበቀ ህፃናት እንዲወለዱ ከማድረግ አንፃርም በሩብ አመቱ 2 ሺህ 678 ህፃናት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ መከናወኑንም ተጠቁሟል፡፡
በመቀጠልም በበጀት ዓመቱ የጤና ሴክተር ትኩረት የሚያደርገው የጤና ተቋማት በማስፋፋትና በግብዓት በሟሟላት የጤና አገልግሎቶች ጥረት ማሻሻል የእናቶችና የህፃናት ሞትን በመቀነስና ዋና ዋና ተላላፊ በሽታዎችና መከላከልና መቆጣጠር ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነት 124 እናቶች የወሊድ አገልግሎት ለመስጠት እቅድ ተይዞ ለ49 እናቶች ብቻ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በተሻለ ሁኔታ ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡
በምክክር መድረኩም የሀዋሣ ክፍለ ከተሞች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN105.html

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር