ዘንድሮ ለሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ዝግጅት እየተደረገ ነው


አዲስ አበባ ጥቅምት 9/2005 (ዋኢማ) - ዘንድሮ የሚካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ግልጽ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ዝግጅቶች እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
የቦርዱ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ይስማ ጅሩ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት ምርጫውን ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ  ለማድረግ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ከወዲሁ እየተከናወኑ ነው።
በተለያየ ደረጃ የነበሩ የምርጫ ጣቢያዎችን በአዲስ መልክ በማደራጀት በኦሮሚያ፤ በትግራይ፤ በአማራና በደቡብ ክልሎች ለሚገኙ የምርጫ አስፈጻሚ አባላት  የአቅም ግንባታ ስልጠናመሰጠቱን  የገለጹት አቶ  ይስማ ለፖለቲካ ፓርቲዎችም በእጩዎች አቀራረብ ዙሪያ  ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል።
የእጩ ተመራጮችና የመራጮች  ምዝገባ እንደዚሁም  ምርጫው የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በመወያየት  ወደፊት እንደሚወሰን አቶ ይሰማ ገልጸዋል።
በአካባቢ ምርጫው የወረዳ፤ የቀበሌ ፤የማዘጋጃ ቤት፤ የከተማ አስተዳደርና የዞን ምክር ቤቶች አባላት እንደሚመረጡ የገለጹት አቶ ይስማ  ምርጫውን በስኬት ለማጠናቀቅ መላው ህብረተሰብ  የበኩሉን ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር