በቅርቡ ከእስር ቤት ወደ ሆስፒታል ስወሰዱ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት የመኪና ግጭት ኣደጋ ደርሶባቸው የነበሩት ካላ ዱካሌ ላሚሶ

በኣደጋ ምክንያት በግንባራቸው ላይ የደረሰባቸውን ጉዳት ፎቶውን ኣጉልተው ይመልከቱ


55 ዓመት እድሜ ባለበት የሆኑት እና በአሁኑ ወቅት በማረሚያ ቤት ሆነው በስኳርና የደም ግፊት እየተሰቃዩ የሚገኙት ካላ ዱካሌ ላሚሶ፣ በነሐሴ 10/2004 .ም ከስራ ቦታቸው ታፍነው እስር ቤት የተወረወሩት፣ እስከዛሬ መስከረም 15/2005 .ም ድረስ ክስ ሳይመሰረትባቸው በማረሚያ ቤት የሚገኙት እና ለሲዳማ ሕዝብ መብት ሕይወታቸውን ሙሉ ሲታገሉ የኖሩ፣በግብርና ዘርፍ ማስተርሳቸውን በእንግሊዝ ሀገር በ1980ዎቹ ያገኙት አቶ ዱካሌ ላሚሶ መስከረም 14/2005 .ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ በቴክኒክና ሞያ ት/ቤት አካባቢ ከወህኒ ቤት በፖሊስ ታጅበው ለደም ግፊት ህክምና ወደ ሃዋሳ ሬፈራል ሆስፒታል ሄደው ሲመለሱ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከተጫኑበት ባጃጅ ጭምር ታርጋ በሌለው መኪና ተገጭተው 4 ሜትር በሚረዝመው የአስፋልት ጠርዝ ገደል ውስጥ ጥለዋቸው ለጊዜው ተሰውረዋል፡፡በዚህም አደጋው በደረሰበት አካባቢ ህብረተሰብ ርብርብ ሕይወታቸው የተረፈ ሲሆን ታርጋ የሌለው ተሸከርካሪም ለጊዜው ተሰውሯል፡፡ 

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር