የ2005 ምርጫን ነፃ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ ቅንጅታዊ ስራ ተጠየቀ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2005 ዓ.ም በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎችና በሁለቱ የከተማ መስተዳድሮች የሚካሄደው ምርጫ ነፃ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ ፥የፍትህ አካላት ቅንጅታዊ ስራ ተጠየቀ።
የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና ለኦሮሚያ ክልል የፍትህ አካላት የተዘጋጀውን ስልጠናውን ሲከፍቱ እንዳስገነዘቡት ፥ በአካባቢ ምርጫ በሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሊከሰት የሚችለውን ቅሬታ ፍትሀዊ መፍትሔ መስጠት እንዲቻል ፥ ተሻሽሎ የወጣውን የምርጫ ደንብና ህግ ፥ የፍትህ አካላት ጠንቅቀው ማወቅ ይጠበቅባቸዋል።
ባለፉት ምርጫዎች እየተሻሻለ የመጣውን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በያዝነው አመትም ይበልጥ እንከን የለሽ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ የፍትህ አካላት በቦርዱ የተዘጋጀውን የምርጫ ሕግና ደንብ ተግባራዊ ማድረጋቸው የጎላ ድርሻ ይኖረዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
Comments
Post a Comment