ቅድስት ማርያም ኮሌጅ ለአስራ ሶስተኛ ጊዜ በተከታታይ ርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፤ እንኳን ደስ ኣላችሁ የሲዳማ ተመራቂዎች

New
አዲስ አበባ መስከረም12/2005 ቅድስተ ማርያም ኮሌጅ በዲግሪ ፣በዲፕሎማ እና በሰርተክፌት መርሀ ግብር ያስተማራቸውን 3 ሺ 325 ተከታታይ የርቀት ትምህርት ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ እና በሀዋሳ ከተሞች አስመረቀ። ምሩቃኑ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በቢዝነስ 1 ሺህ 498፣ በመምህራን ትምህርት ፕሮግራም 76፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ፕሮግራም በደረጃ 4 መርሀ ግብር 1ሺህ 430 በደረጃ አራት ደግሞ 319 ተማሪዎች ናቸው ። ኮሌጅ ለአስራ ሶስተኛ ጊዜ በተከታታይ ርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ተማሪዎች ባስመረቀበት ፕሮግራሙ ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ወንደሰን ታምራት ባደረጉት ንግግር ምሩቃኑ የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር በመለወጥ ለሀገራቸው ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፆኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ። በክብር እንግድነት የተገኙት ታዋቂው የግብርና ሳይንስ ተመራማሪ ዶክተር ስሜ ደበላ ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎቹ ስራ ጠባቂ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ በመሆን ራሳቸውንም ሌሎችንም ዜጎች መጥቀም እንደሚገባቸው ተናግረዋል ። በተለይ በቴክኔክና ሙያ ዘርፍ ተመራቂዎች በግብርና ዘርፍ ላይ ቴክኖሎጂዎችን በሰፋት በመጠቀም ኋላ ቀር የግብርና አሰራሮችን ለማስወገድ በሚደረገው ስራ ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይኖርባቸዋል ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል ።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር