ከተለያዩ የሲዳማ ዞን ወረዳዎች የተወጣጡ ሰዎች ለኣቶ መለሰ ዜናዊ በሲዳማ ባህል መሰረት እንጨት ተክሎ ማልቀሳቸው ተሰማ

በትናንትናው እለት ቁጥራቸው ከሶስት ሺ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ዞን ነዋሪዎች በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ለኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ መለስ ዜናዊ በሃዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል መሰረት ኣልቅሰዋል።

በሲዳማ ባህል መሰረት ለጀግና እንደምለቀሰው ሁሉ ለኣቶ መለሰ ዜናዊም እንጨት ተተክሎ ቀይ ተቀብቶ የተለቀሰላቸው ሲሆን፤  'ጎባ ባኢታ ኣና ሆጌ' እያለ በቄጣላ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።

በሃዘን መግለጫ ስነስርዓቱ ላይ ከሽማግሌዎች የተወከሉ እና የክልል መንግስቱ ባለስልጣናት ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸው በኣቶ መለሰ ዜናዊ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ከዳር እንዲደርሱ ሁሉም በጋራ እንዲሰራ ጥር ኣቅርበዋል።

በስነስርዓቱ ላይ የክልል እና የሲዳማ ዞን ባላስልጣናትን ጨምሮ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እና መንግስት ባዘጋጃቸው መኪኖች ባህላዊ ልብስ እንዲለብሱ ተደርገው ከየወረዳዎቹ የተጋበዙ ሰዎች መገኘታቸውን ወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ ዘግቧል ።  

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር