ኢትዮጵያ ከሶስት አመት በኋላ በምግብ ዋስትና ራሷን እንደምትችል ተጠቆመ


አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 4፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከሶስት አመት በኋላ በምግብ ዋስትና ራሷን እንደምትችል የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሰረት የዛሬ ሶስት አመት፤ ከ400 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የግብርና ምርት በዓመት የማምረት አቅም ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል።

ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው ይህን እቅድ ለማሳካት የሚያስችል አሰራር እየተዘረጋ መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።

እቅዱ በይፋ በተጀመረበት በ2003 ዓመተ ምህረት ከዋና ዋና ሰብሎች የተገኘው 203 ሚሊዮን ኩንታል የግብርና ምርት በልማት እቅዱ ከተቀመጠው የዘጠኝ በመቶ እድገት አሳይቷል።

በተመሳሳይ በ2004 ዓመተ ምህረት 218 ሚለዮን ኩንታል የምርት መጠን ለማግኘት ታስቦ እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት መቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።    

ለእቅዶቹ መሳካት ደግሞ በዋነኝነት አርሶ አደሩን በልማት ሰራዊት በማደራጀት ንቅናቄ መፈጠሩ በምክንያትነት ተቀምጧል።

በቀጣይነት ይህን የተደራጀውን አርሶ አደር አቅም መገንባት ከተቻለም እቅዱን ለማሳካት አያዳግትም ባይ ናቸው።

በኢትዮጵያ አምስት ሚሊዮን ሄክታር የሚደርሰው መሬት በመስኖ ሊለማ ይችላል።

ከዚህ ውስጥ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር ያህሉ በአነስተኛ መስኖ የሚለማ ሲሆን ፥ ቀሪው ደግሞ በመካከለኛና በከፍተኛ መስኖ ሊለማ የሚችል ነው።

አሁን እየታየ የሚገኘው የምግብ እህል የዋጋ ንረትም እንደሚረጋጋ ጠቁመው ፥ በመንግስት በኩል ይህን የዋጋ ማሻቀብ ለመቀልበስ ዋና ዋና የግብርና ምርቶች ወደ ውጭ እንዳይላኩ ከመከልከል ጨምሮ ብዙ የፖለሲ እርምጃዎች እንደተወሰዱ መናገራቸውን ታደሰ ብዙአለም ዘግቧል።
 http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=25312&K=

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር