ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው



ሀዋሳ ፣ ሀምሌ 20፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ሃዋሳ የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ልትጀምር ነው።

በቅርቡም አራት አውቶብሶች ገብተው ስራ እንደሚጀምሩ ነው የከተማዋ አስተዳደር  ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት  የገለፀው ።

አውቶብሶቹ ከከተማዋ ውጭ ለሚገኙ አዋሳኝ ከተሞችም የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ ።

የከተማዋ አስተዳደር እንደሚለው ለነዋሪዎች የትራንስፖርት አማራጭ ከመስጠትም ባለፈ በከተማዋ ቀስ በቀስ ደረጃቸውን በጠበቁ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማቅረብ ያስችላል ።

አውቶብሶቹን ስራ ለማስጀመር 24 የማቆሚያ ፌርማታዎች ተለይተዋል።

በአሁኑ ወቅት በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከ3 ሺህ በላይ የሚበልጡ ተሽከርካሪዎች ሲኖሩ ፥ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ ባጃጆች ናቸው።

የአስተዳደሩ የትራንስፖርት ፅህፈት ቤት እንደሚለው የአውቶብሶቹ ወደ ከተማዋ መግባት ነዋሪው አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኝ ያስችላል ፤ ዘገባው የታደሰ ብዙዓለም ነው።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር