ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ:


ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ::በሀዋሣ ከተማ የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከፍተኛ ሁለት ዐ3 ቀበሌ መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ከሳውዲን ተራድኦ ድርጅት ኘሮጀክት ጋር በመተባበር ለ145 ወላጅ አጥና ችግረኛ ህፃናት የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል::
የኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሣ ቅርንጫፍ ሥራ አስያኪጅ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት ህፃናቱ ቀደም ሲል የትምህርት ፣ የጤናና የስነ ልቦና ድጋፍ ሲሰጣቸው የቆዩ ናቸው::ከፍተኛ ሁለት ዐ3 መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከድርጅታቸው ጋር በመተባበር የሚያደርግላቸውን ድጋፍ በመጠቀም ህፃናቱ በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል::
የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ ወይዘሮ ዘውዲቱ ገ/መስቀል በበኩላቸው የመረዳጃ እድርና ልማት ማህበሩ ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመተባበር  በክፍለ ከተማው በዓላትን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለወላጅ አጥና ችግርተኛ ህፃናት የተለያዩ ድርጋፎችን  እንደሚያደርግ ተናግረዋል::
የአሁኑ ተረጂ ህፃናት በሚደረግላቸው ድጋፍ ተግተው ከተማሩ የነገይቱ አገር ተረካቢና የተሻለ ዜና መሆን እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡ ባልደረባችን ጌታሁን አንጭሶ እንደዘገበው::

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር