Posts

Showing posts from December, 2011

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ ፕሮግራም በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ ሊከፍት ነው

Image
የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሶሻል አንትሮፖሎጂ ፕሮግራም በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ ሊከፍት ነው አዋሳ, ታህሳስ 13 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በብሄር ብሄረሰቦች ልማት ላይ ያተኮረ የሶሻል አንትሮፖሎጂ የትምህርት ፕሮግራም በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመክፈት መዘጋጀቱን ገለጸ፡፡ የፕሮግራሙ መከፈት ለሀገሪቱ ህዝቦች ባህልና ቋንቋ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንዳለው የደቡብ ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ለማ ገዙሜ ገልጸዋል፡፡ ለፕሮግራሙ የተዘጋጀውን ስርዓተ ትምህርት ለመገምገም ከአሜሪካ የመጡና የሀገር ውስጥ ከፍተኛ ባለሙያዎች ትናንት ለግማሽ ቀን ባካሄዱት አውደ ጥናት ላይ የዩኒቨርሰቲው ፕሬዜደንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት አንዳንድ ቋንቋዎችና ባህሎች ሳይታወቁ የሚጠፉበት ሁኔታ እንዳለ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ ፕሮግራሙ ይህንን ችግር ከመቅረፍ ባሻገር የክልሉና የሀገሪቱን ብሄር ብሄረሰበችን ባህል ፣ ቋንቋ ፣ ወግ ፣ ታሪክና ዕድገት በማጥናት ፣ በመንከባከብና በማልማት ጠብቆ ለማቆየት ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር አስታውቀዋል፡፡ በክልሉ ዋና ከተማ የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ከመጪው የካቲት 2004 ጀምሮ የሚከፍተው ፕሮግራም በተለይ በደቡብ የሚገኙትን ከ56 በላይ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቋንቋዎች ፣ባህሎች ሀይማኖቶች ፣ወጎችና ታሪካዊ እሴቶች በዘላቂነት ለማልማት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው የክልሉን የሰው ሃይል አቅም ከመገንባት ባሸገር ፖሊሲዎችንና ውሳኔዎችን ለማስተዋወቅ ከክልሉ መንግስትና የብሄረሰቦች ምክር ቤት ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ለማ ገዙሜ በበኩላቸው ዩኒቨርስቲው በሁለተኛ ድግሪ ደረጃ የሚከ

Construction of fish farms underway in Hawassa

Image
Hawassa, December 17, 2011 (Hawassa) - Construction of fish farms underway in Hawassa  and Arbaminch towns of South Ethiopia Peoples State with an outlay of over 4.8 million Birr, the State's Agriculture Bureau said. Bureau Communication Affairs Process Owner, Birhanu Tofu told ENA that both projects could produce over 700,000 young fish a year. He said the construction of the Hawassa’s farm is expected to be completed in this Ethiopian budget year. Procurement is underway for the farm with 1.5 million Birr. The farms would restore the depleted fish potentials of the areas.

Authority repairing 265-km Addis -Modjo-Hawassa Road

Image
Addis Ababa, December 18, 2011 (Addis Ababa) - The 265-km Addis Ababa-Modjo-Hawassa Road is being repaired with nearly 170 million Birr, the Ethiopian Roads Authority said. Communication Director with the Authority, Samson Wondimu said the road constructed ten years before was damaged due to heavy traffic. Samson said the Authority has set plan to undertake heavy maintenance on 5-km alleys in Modjo Town with seven million Birr in the current Ethiopian budget year. The government will cover the cost for the maintenance of the road, he said.

በቡና አላላክ ላይ የወጣው አወዛጋቢ መመርያ ተሻረ

Image
ንግድ ሚኒስቴር ከህዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ሌላ የተለየ ፈቃድ ከሚኒስቴሩ ካልተሰጠ በስተቀር የኢትዮጵያ ቡና በብትን በኮንቴይነር እንዲላክ ያወጣውን አወዛጋቢ መመርያ ማንሳቱን አስታወቀ፡፡ መመርያው ተግባራዊ እንዲሆን በተወሰነ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነው የተሻረው፡፡   የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ ባለፈው ሐሙስ የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማኅበር የቦርድ አባላትን ሰብስበው ካነጋገሩ በኋላ፣ ቡና በብትን ብቻ ይላክ የሚለው መመርያ ተቀልብሶ በጆንያና በብትን መላክ እንደሚቻል መፈቀዱን ነግረዋቸዋል፡፡  ቡና ላኪዎቹ በበኩላቸው ምንም እንኳ በብትን መላኩ በሚያስገኘው ጠቀሜታ ላይ ጥያቄ ባይኖራቸውም፣ ገዢዎች እስኪቀበሉትና ፍላጎት ኖሯቸው በብትን መቀበል መፈለጋቸውን እስኪያስታውቅ፣ ለብትን አላላክ ሥርዓት የሚያስፈልጉ መሠረተ ልማቶች እስኪሟሉ ድረስ ግን በብትንም በጆንያም መላክ ሊፈቀድ እንደሚገባ ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡  በብትን የመላክ መመርያው የተነሳው እነዚህን እውነታዎች ከግምት በማስገባት እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል፡፡ መመርያው ከተነሳ በኋላ በብትን መላክ እስኪለመድና ተቀባይነት እስኪያገኝ ድረስ በጆንያ መላኩ እንደ ሽግግር ወቅት ተደርጎ ቢፈቀድም፣ ይህ የሽግግር ወቅት የተባለው በጊዜ ገደብ አለመቀመጡን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡  ለመመርያው መውጣት ሲሰጡ ከነበሩ ምክንያቶች አንዱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አምነውበት ተቀባይነት ያገኘ አሠራር በመሆኑ፣ የዝግጅት ጊዜው አምና ተጠናቆ ዘንድሮ ሙሉ ለሙሉ ወደ ትግበራ ሊገባበት እንደተቻለ መሆኑን ንግድ ሚኒስቴር ለሁሉም ላኪዎች ያሰራጨው ደብዳቤ ያመለክታል፡፡  በሚኒስትር ዴኤታው አቶ ያዕቆብ ያላ ተፈርሞ የወጣው መመርያ እንደሚያትተው፣ ቡናን በብትን በኮንቴይነር ውስጥ አሽጎ መላክ የኢ

በሃዋሳ ከተማ የተተከለ ዘመናዊ የተሸከርካሪ አካል ብቃት መመርመሪያ ማሽን ስራ ጀመረ

Image
አዋሳ, ታህሳስ 7 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክለል ከአምስት ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገዛ ዘመናዊ የተሸከርካሪ ብቃት መመርመሪያ ማሽን በሃዋሳ ከተማ ተተክሎ ስራ መጀመሩን የክልሉ የትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ የስራ ሂደት ተወካይ አቶ አረጋ አዊቶ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት የሚደርሰውን የህይወት መጥፋትና ንብረት ውድመት ለመቀነስ መሳሪያው ከፍተኛ እሰተዋጽኦ አለው ፡፡ ቢሮው በሃዋሳ ከተማ በትራንስፖርት ዘርፍ ተደራጅተው ከሚንቀሳቀሱ የግል ባላሃብቶች ጋር በመቀናጀት የገዛው የመመርመሪያ ማሽን የተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ አሰጣጥ ስርዓቱን ዘመናዊ በማድረግ በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት ምክንያት የሚደርሰውን አደጋ በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል፡፡ ማሽኑ በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መተከሉን የጠቆሙት ተወካዩ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ስራ ላይ ውሎ ውጤታማነቱ መረጋገጡን በተደረገው የልምድ ልውውጥ ማወቅ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የሚገኙ ከ35ሺህ የሚበልጡ ተሽከርካሪዎች መካከል አብዘኛዎቹ የተሽከርካሪ ምርመራ በተፈለገው መጠን እንደማይደረግ በመታወቁ ማሽኑ መተከሉን ገልጸው በዘርፉ ይከሰት የነበረውን ችግር ከ70 በመቶ በላይ እንደሚቀርፍም አስታውቀዋል፡፡ ቀደም ሲል በእይታ በሚደረግ የቴክኒክ ምርመራ በቀን ከአምስት የማይበልጡ ተሽከርካሪዎች እንደሚስተናገዱ ጠቁመው በማሽን በሚደረገው ምርመራ ግን በቀን እስከ 30 ተሽከርካሪ በመመርመር ብቃት የማረጋገጥ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ለእንድ ተሽከርካሪ ከአንድ ሰዓት በላይ የሚፈጅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የ

ቢሮው በ9 ሚሊዮን ብር ወጪ የትምህርት ሥርጭት መቀበያ ዲሾች ግዥና ተከላ አካሄደ

Image
ሀዋሳ፤ ታህሳስ 6/2004/ዋኢማ/ - የደቡብ ክልል በ9 ሚሊዮን ብር የትምህርት ሥርጭት መቀበያ ዲሾች ግዥና ተከላ ማካሄዱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቀው፤ የትምህርት ሥርጭት  መቀበያ ዲሾች ተከላ  የተካሄደው በክልሉ አዲስ ለተከፈቱ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች ነው። በትምህርት ቤቶቹ የሳተላይት ዲሾች ተከላ መካሄድ በፕላዝማ ከማዕከል የሚተላለፉ ትምህርቶችን በጥራት ለማድረስ እንደሚያስችል በቢሮው የመንግሥት ኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን የሥራ ሂደት ባለቤት አቶ ደረሰ ጋቲሶ ገልጸዋል። በተለይም ተማሪዎች በአካባቢያቸው የማይገኙ የሳይንስ የሙከራ ናሙና ቁሳቁሶችንና ሂደቶቻቸውን በቀላሉ በፕላዝማ አማካኝነት በመመልከትና በመረዳት የትምህርት ክህሎታቸውን ለማዳበር እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል። በተጨማሪም ትምህርት ቤቶቹ በሳተላይት ዲሾቹ አማካኝነት የሚላክላቸውን በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፉ የትምህርት ፕሮግራሞችን ለተማሪዎች በማቅረብና ቀልጣፋ የመማር ማስተማር ሂደትን በመፍጠር ለትምህርት ጥራት መጠበቅ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው  አስረድተዋል። የሥርጭት መቀበያ ዲሾቹ ከመደበኛ የትምህርት ሥራዎች ጎን ለጎን መምህራንና ተማሪዎች የሳተላይት ዲሾቹን በመጠቀም የተለያዩ ክልላዊና አገራዊ ኮንፍረንሶችን በቀጥታ ለመሳተፍ እንደሚያስችሏቸው የሥራ ሂደት ባለቤቱ ጠቁመዋል። ይህም መምህራን ተማሪዎችና ሌሎች የትምህርት ቤቶቹ ማህበረሰቦች ወቅታዊ መረጃዎች በማግኘት ለትምህርት ሥራዎች መጎልበት የበኩላቸውን ለመወጣት የሚያስችላቸውን ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርላቸው የሥራ ሂደት ባለቤቱን መግለፃቸውን ጠቅሶ የዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘገባ ያመለክታል።

National Geographic MapGuide Launched

Addis Ababa, December 16, 2011 (Addis Ababa) - The National Geographic MapGuide designed to showcase to the national and international audiences the natural and cultural attractions that define the Central and Southern Rift Valley areas was launched here on Thursday. Director-General of the Authority for Research and Conservation of Cultural Heritage with the Ministry of Culture and Tourism, Yonas Desta on the occasion said the MapGuide will fill the tourism information gap in the country. The MapGuide is the first in Ethiopia and the second Geo-Tourism MapGuide in Africa, the director said. Efforts are underway to expand such kind of activities to other attraction sites of the country, he said, adding, currently, 10,000 copies of the MapGuide have been readied to be distributed among tourists. He also lauded USAID and Ethiopian Sustainable Tourism Alliance (ESTA) as well as the Horn of Africa Regional Environment Centre for taking the initiative in helping to develop

በሃዋሳ ከተማ የተተከለ ዘመናዊ የተሸከርካሪ አካል ብቃት መመርመሪያ ማሽን ስራ ጀመረ

Image
Hawassa Bus station Area አዋሳ, ታህሳስ 7 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክለል ከአምስት ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገዛ ዘመናዊ የተሸከርካሪ ብቃት መመርመሪያ ማሽን በሃዋሳ ከተማ ተተክሎ ስራ መጀመሩን የክልሉ የትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ የስራ ሂደት ተወካይ አቶ አረጋ አዊቶ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት የሚደርሰውን የህይወት መጥፋትና ንብረት ውድመት ለመቀነስ መሳሪያው ከፍተኛ እሰተዋጽኦ አለው ፡፡ ቢሮው በሃዋሳ ከተማ በትራንስፖርት ዘርፍ ተደራጅተው ከሚንቀሳቀሱ የግል ባላሃብቶች ጋር በመቀናጀት የገዛው የመመርመሪያ ማሽን የተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ አሰጣጥ ስርዓቱን ዘመናዊ በማድረግ በተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ጉድለት ምክንያት የሚደርሰውን አደጋ በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ እንደሚረዳም ጠቁመዋል፡፡ ማሽኑ በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ መተከሉን የጠቆሙት ተወካዩ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ስራ ላይ ውሎ ውጤታማነቱ መረጋገጡን በተደረገው የልምድ ልውውጥ ማወቅ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የሚገኙ ከ35ሺህ የሚበልጡ ተሽከርካሪዎች መካከል አብዘኛዎቹ የተሽከርካሪ ምርመራ በተፈለገው መጠን እንደማይደረግ በመታወቁ ማሽኑ መተከሉን ገልጸው በዘርፉ ይከሰት የነበረውን ችግር ከ70 በመቶ በላይ እንደሚቀርፍም አስታውቀዋል፡፡ ቀደም ሲል በእይታ በሚደረግ የቴክኒክ ምርመራ በቀን ከአምስት የማይበልጡ ተሽከርካሪዎች እንደሚስተናገዱ ጠቁመው በማሽን በሚደረገው ምርመራ ግን በቀን እስከ 30 ተሽከርካሪ በመመርመር ብቃት የማረጋገጥ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ለእንድ ተሽከርካሪ ከአንድ

Debub Global to start in January

Image
Debub Global Bank is to become the newest entrant to the banking sector in the new year. According to an official of the bank, 286 million birr of the 300 million birr it had planned to raise as subscribed capital has been locked so far and they have managed to sell about 150 million birr in paid up capital. Shares amounting to 5,481 have been purchased and presented to the National Bank of Ethiopia and are awaiting signature and verification from shareholders. The official said that the bank, which had a general assembly meeting held in the presence of NBE officials on September 20, 2010 at the Addis Ababa Millennium Hall has nominated some 30 potential people to sit on its board of directors; which will make up a dozen seats.  He also said they have been waiting for six months to start banking operations after fulfilling the necessary criteria. It is also done to avoid the controversies that happened recently in other banks that have been accused of nepotism and favoriti

Awash Bank Picks Design Champs for Hawassa Branches

Image
Winning designs for Hawassa (left), Balcha Aba Nefso (centre), and Bulbula (right), branches, were all selected as winners by jury members based on criteria that included urban context, site use, and representation of Awash. The first private bank to construct its own headquarters, Awash International Bank (AIB), selected three designs for branches to be located in Addis Abeba and Hawassa, Southern Regional State on Thursday, December 8, 2011. During a ceremony at the Hilton Hotel, the winning designs for the branches to be constructed around Bole Bulbula, Balcha Aba Nefso, and Hawassa, 273km south of the capital, were selected out of 14 entries. A total of six companies took part in the competition. Gereta Consult, MH Engineering, and Yohannes Abay Plc, competed for all three branch designs, while Zeleke Belay Plc and Age Plc each submitted designs for the Hawassa and Balcha Aba Nefso sites. Studio 7 Architects Plc limited itself to one, competing for the Bole Bulbula de

የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ ከ100 የሚበልጥ የምርምር ፕሮጀክቶች እያካሄደ ነው

Image
አዋሳ, ህዳር 28 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ችግር ፈቺ የሆኑ ከ100 የሚበልጡ የምርምር ፕሮጀክቶች እያካሄደ መሆኑን የዩኒቨርስቲው የምርምር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ገለጹ። ዳይሬክቴሩ ዶክተር ተስፋዬ አበበ ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ በተካሄደ የምርምር ስራ ግምገማ አውደ ጥናት ላይ እንዳስታወቁት የምርምር ፕሮጀክቶቹ በተለይ ሀገሪቱ ለተያያዘችው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን የልማት ፕሮግራም ስኬት የበኩላቸውን አሰተዋጾኦ የሚያበረክቱ ናቸው፡፡ ቀደም ብሎና ዘንድሮ የተጀመሩት የምርምር ፕሮጀክቶች በግብርና ፣ በተፈጥሮ ሀብት ፣ በደን ልማት ፣ በእንስሳት ልማት፣ በጤናና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ የምርምር ስራዎቹ የሚካሄዱት ከደቡብ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር በሀዋሳ ከተማና ዙሪያ፣ በቦርቻ ፣ በወንዶ ገነት፣በዳሌ ፣በሃገረ ሰላምና ሌሎች አካባቢዎች መሆኑን ጠቁመው በዩኒቨርስቲው የሚያስተምሩ የየዘርፉ ምሁራንና ተመራቂ ተማሪዎችን በማንቀሳቀስና ህብረተሰቡን በማሳተፍ ሁሉንም የልማት መስኮችን የዳሰሱ ችግር ፈቺ መሆናቸውን ገልጠዋል፡፡ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ በግብርናው ዘርፍ ለዝናብ አጠር አካባቢ ተስማሚና ውጤታማ የሆኑ አዳዲስ የበቆሎ የእንሰት ፣የስራ ስርና ሌሎች የምግብ ሰብል ዓይነቶች በምርምር በማውጣት ለተጠቃሚው ለማድረስ በሂደት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው ፕሬዜዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በበኩላቸው የመማር ማስተማሩን ስራ በጥራትና በፍትሃዊነት ከማራመድ ጎን የሚካሄደው ምርምር ከውጪ ሀገራት መሰል የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር መሆኑን ገልጸዋል። ምርምሮችን በማስፋትና ግኝቶችን ወደ ምርት ስራ በማሸጋገር የተሻለ

የኢትዮጵያ ዋነኛ ቡና ገዥዎች ለመንግሥት ተቃውሟቸውን አሰሙ

Image
-    ቡና ላኪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አቤቱታ ሊያቀርቡ ነው የኢትዮጵያ ቡና ገዥ ከሆኑት መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱት የስዊዘርላድንና የጀርመን ኩባንያዎች በማኅበሮቻቸው በኩል ለኢትዮጵያ ኤምባሲዎች፣ ለውጭ ጉዳይና ለንግድ ሚኒስቴር የተቃውሞ ደብዳቤ መጻፋቸው ታወቀ፡፡ የእንግሊዝ ኩባንያዎችን ጨምሮ አሥር ታዋቂ የኢትዮጵያን ቡና የሚገዙ ማኅበራት በብትን እንደማይገዙ ያሳወቁ ሲሆን፣ ፊታቸውን ወደ ሌሎች ቡና ሻጮች ማዞራቸውም እየተነገረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የኮሎምቢያና የኬንያ ቡና ላኪዎች የአረቢካ ቡና ገበያን ሊቆጣጠሩት እንደቻሉ፣ በዚህ ሳምንት ብቻ ኢትዮጵያ ልትሸጥ የሚገባት 30 ሺሕ ቶን የሚገመት ቡና ሳይሸጥ መቅረቱን ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ንግድ ሚኒስቴር ከህዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ያወጣው መመርያ ቡና ገዥዎች እንደተቃወሙትና በኮንቴይነር በብትን እንዲላክልን አንፈልግም ብለውናል በማለት የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ያቀረቡትን ሐሳብ ሚኒስቴሩ ሊቀበለው ባለመቻሉ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአቤቱታ ደብዳቤ ለማቅረብ መገደዳቸውንና በነገው ዕለትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት እንደሚያስገቡ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ከህዳር 1 ቀን ጀምሮ ሁሉም ላኪዎች ቡና በብትን በኮንቴይነር እንዲልኩ የወጣውን መመርያ ቡና ገዥዎች እንዳልተቀበሉት፣ በጆንያ የማይላክላቸው ከሆነ ከኢትዮጵያ ቡና አንገዛም ማለታቸውን ለሚኒስቴሩ ቢያሳውቁም፣ ሳይቀበላቸው በመቅረቱ አሳምናችሁ በብትን እንዲገዙ አድርጉ በማለት ኃላፊነቱን ጥሎባቸዋል፡፡ ከፍተኛ የታጠበ ቡና በጥርና በካቲት ወራት ተጓጉዞ ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ አሁን ውል ሊፈጸም ይገባ እንደነበር የሚገልጹት ቡና ላኪዎች፣ አሁን በሚታየው የዓለም የኢኮኖሚ መዋዠቅ የቡና ኤክስፖርት መቀነሱን ይ

ንግድ ሚኒስቴር የአራት ወራት የቡና ኤክስፖርት አሳስቦኛል አለ

Image
-    ቡና ላኪዎች ይሻሻልልን ያሉትን መመርያ ሳይቀበለው ቀረ ‹‹በብትን ብትልኩ አንቀበልም ብለውናል›› ቡና ላኪዎች ‹‹በብትን የሚላከው በጃፓን ገበያ የደረሰብንን ካየን በኋላ ነው›› አቶ ያዕቆብ ያላ  ንግድ ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት የቡና ኤክስፖርት አፈጻጸምን በተመለከተ ከላኪዎች ጋር ባካሄደው ስብሰባ፣ ሊላክ ከሚገባው ቡና በታች በመላኩ እንዳሳሰበው አስታወቀ፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ያዕቆብ ያላ ላኪዎችን ጠርተው እንመካከር ባሉበት ህዳር 28 ቀን 2004 ዓ.ም. ስብሰባ ላይ እንዳስታወቁት፣ በአራት ወራት ውስጥ ሊላክ የሚገባው ቡና ባለመላኩ ሰባት ወራት ብቻ ለቀረው የበጀት ዓመቱ ኤክስፖርት አፈጻጸም አሳሳቢ ነው፡፡ ‹‹የቀረን ሰባት ወር ነው፡፡ በዚህ ዓመት ከቡና 1.1 ቢሊዮን ዶላር እየተጠበቀ ነው፡፡ ይህ የአገሪቱ ዕቅድ ነው፡፡ ችግሮቹ በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ ይህንን ሁኔታ ይጐዳሉ፤›› በማለት አቶ ያዕቆብ አሳስበዋል፡፡ ለዓለም ገበያ መቅረብ ይገባው የነበረው የቡና መጠን የቀነሰው በተለያዩ ችግሮች መሆኑን የገለጹት ነጋዴዎቹ፣ በተለይ ቡና በብትን እንዲላክ በወጣው መመርያ መሠረት ለመላክ ባለመቻላቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ንግድ ሚኒስቴር ላለፉት አራት ወራት ለውጭ ገበያ ይላካል ያለው የቡና መጠን ከ66,400 ቶን በላይ ነበር፡፡ ነገር ግን የተላከው ቡና ከ44,029 ቶን በላይ ባለመሆኑ ከ22,371 ቶን በላይ ቡና ሳይላክ ቀርቷል፡፡ በጥቅምት ወር መላክ የነበረበት 75 ሺሕ ቶን ቢሆንም፣ ሊሰበሰብ የተቻለው 13 ሺሕ ቶን ነበር፡፡ ያም ሆኖ ግን ወደ ውጭ የተላከው አራት ሺሕ ቶን ብቻ ይሆናል፡፡ ቡናው እንደታሰበው ሊላክ ያልተቻለው ደግሞ ቡናው በውል ከተሸጠ በኋላ በወቅቱ ሊላክ ባለመቻሉ (የተሸጡ ኮንትራቶች ስላልተፈጸሙ)፣ በም

በሲዳማ ዞን ከ42 ሺህ ቶን የሚበልጥ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ሊቀርብ ነው

Image
አ ዋሳ, ታህሳስ 4 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን በያዝነው የምርት ዘመን ከ42 ሺህ ቶን የሚበለጥ እሸት ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የዞኖ ግብይትና ህብረት ስራ መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ ቡርቃ ቡላሾ እንዳስታወቁት ከዞኑ ለገበያ የሚቀርበውን የቡና ምርት በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በበጀት ዓመቱ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ 42ሺህ 680 ቶን እሸት ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸው ከዚህም ውስጥ 41ሺህ 285 ቶን ያህሉ የታጠበ እሸት ቡና ነው ብለዋል፡፡ ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበው እሸት ቡና ካለፈው ዓመት በ12ሺህ 682 ቶን ብልጫ እንዳለው ገልጸው ለስራው ስኬት በበጀት ዓመቱ ብቻ 64 ማህበራትና 92 የግል ባለሃብቶች በግብይት እንዲሰማሩ መደረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ ለቡና ጥራት መበላሸት መነሻ የሆኑ ህገ ወጥ የቡና ዝውውርና ሌሎች ችግሮችን ለመቆጣጠርና ዕቅዱን ለማሳካት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረ ሃይል በማቋቋም እስከ ቀበሌ ድረስ የቁጥጥር የክትትክልና የድጋፍ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም 214 ደረጃቸውን የጠበቁ የግብይት ማዕከላት በማቋቋም ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን የመቆጣጠርና ነፃና ፍትሃዊ የገበያ ስርዓት እንዲሰፍን የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡ ከዞኑ 19 ወረዳ አብዛኛዎቹ ቡና አብቃይ በመሆናቸው ለገበያ የሚቀርበው ቡና ጥራት ለማሻሻል ለማህበራትና አርሶ አደሮች በቡና ጥራት አጠባበቅና ህገ ወጥ ንግድ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱን ገልጸው አንዳንድ ማህበራት በአዲስ ቴክኖሎጂ የተሰሩ የቡና መፈልፈያ መጠቀም መ

Sidamu sumuda

Image
New

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የመስኖ አጠቃቀም ዘዴዎችን ለአርሶ አደሮች እያስተዋወቀ ነው

Image
ሀዋሳ፤ ህዳር 30/2004/ዋኢማ/  - ዘመናዊ የመስኖ አጠቃቀም ዘዴዎችን ለአርሶ አደሩ ለማስተዋወቅ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው የመስኖ ልማትና ውሃ አጠቃቀም ምህንድስና ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ወሰኑ ለማ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ፕሮጀክቱ ካለፈው ጥቅምት ጀምሮ በደቡብ ክልል በተመረጡ ዝናብ አጠር አካባቢዎች ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል። ዘመናዊ የመስኖ አጠቃቀም ዘዴ ፕሮጀክቱን ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅ ሥራ የሚሰራው ከኢትዮጵያ የውሃ ሀብት አጠቃቀም ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር መሆኑ ተገልጿል። ፕሮጀክቱ አርሶ አደሩ የጎርፍ ውሃን በማሰባሰብና የከርሰ ምድር ውሃን በቀላሉ በማውጣት ለእርሻ ሥራዎች ሊያውል የሚችልባቸውን ዘዴዎች እንደሚያስተዋውቅ የትምህርት ክፍል ኃላፊው አመልክተዋል። ፕሮጀክቱ እየተካሄደ የሚገኘው ዩኒቨርሲቲው በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በሥሩ ባቋቋማቸው ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮች አማካኝነት መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ይህም አርሶ አደሩ በፕሮጀክቱ አማካኝነት በንድፈ ሀሳብና በተግባር የሚሰጡ ሥልጠናዎች በቅርበት ለመከታተል እንደሚያስችለው ተናግረዋል።  ለሦስት ዓመት የሚቆየው ይኼው ፕሮጀክት በ14 የገበሬዎች የሕብረት ሥራ ማህበራት ሥር የተደራጁ ከ8ሺ በላይ አባወራ አርሶ አደሮችን የመስኖ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ አስረድተዋል።  ፕሮጀክቱ በዝናብ አጠር አካባቢዎች የሚገኙ አርሶ አደሮች የመስኖ አማራጮችን ተጠቅመው፤ በዓመት ከሁለት እስከ ሦስት ጊዜ በማምረት በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸው የምግብ እጥረት ለመቅረፍ እንደሚያስችላቸው ኃላፊው አመልክተዋል። ዩኒቨርሲቲው ከመደበኛ የመማር ማስተማር ሥራዎቹ በተጨማሪ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር ችግ

ንግድ ሚኒስቴር የአራት ወራት የቡና ኤክስፖርት አሳስቦኛል አለ

-    ቡና ላኪዎች ይሻሻልልን ያሉትን መመርያ ሳይቀበለው ቀረ ‹‹በብትን ብትልኩ አንቀበልም ብለውናል›› ቡና ላኪዎች ‹‹በብትን የሚላከው በጃፓን ገበያ የደረሰብንን ካየን በኋላ ነው›› አቶ ያዕቆብ ያላ  ንግድ ሚኒስቴር ባለፉት አራት ወራት የቡና ኤክስፖርት አፈጻጸምን በተመለከተ ከላኪዎች ጋር ባካሄደው ስብሰባ፣ ሊላክ ከሚገባው ቡና በታች በመላኩ እንዳሳሰበው አስታወቀ፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ያዕቆብ ያላ ላኪዎችን ጠርተው እንመካከር ባሉበት ህዳር 28 ቀን 2004 ዓ.ም. ስብሰባ ላይ እንዳስታወቁት፣ በአራት ወራት ውስጥ ሊላክ የሚገባው ቡና ባለመላኩ ሰባት ወራት ብቻ ለቀረው የበጀት ዓመቱ ኤክስፖርት አፈጻጸም አሳሳቢ ነው፡፡ ‹‹የቀረን ሰባት ወር ነው፡፡ በዚህ ዓመት ከቡና 1.1 ቢሊዮን ዶላር እየተጠበቀ ነው፡፡ ይህ የአገሪቱ ዕቅድ ነው፡፡ ችግሮቹ በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ ይህንን ሁኔታ ይጐዳሉ፤›› በማለት አቶ ያዕቆብ አሳስበዋል፡፡ ለዓለም ገበያ መቅረብ ይገባው የነበረው የቡና መጠን የቀነሰው በተለያዩ ችግሮች መሆኑን የገለጹት ነጋዴዎቹ፣ በተለይ ቡና በብትን እንዲላክ በወጣው መመርያ መሠረት ለመላክ ባለመቻላቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ንግድ ሚኒስቴር ላለፉት አራት ወራት ለውጭ ገበያ ይላካል ያለው የቡና መጠን ከ66,400 ቶን በላይ ነበር፡፡ ነገር ግን የተላከው ቡና ከ44,029 ቶን በላይ ባለመሆኑ ከ22,371 ቶን በላይ ቡና ሳይላክ ቀርቷል፡፡ በጥቅምት ወር መላክ የነበረበት 75 ሺሕ ቶን ቢሆንም፣ ሊሰበሰብ የተቻለው 13 ሺሕ ቶን ነበር፡፡ ያም ሆኖ ግን ወደ ውጭ የተላከው አራት ሺሕ ቶን ብቻ ይሆናል፡፡ ቡናው እንደታሰበው ሊላክ ያልተቻለው ደግሞ ቡናው በውል ከተሸጠ በኋላ በወቅቱ ሊላክ ባለመቻሉ (የተሸጡ ኮንትራቶች ስላልተፈጸሙ)፣ በምርት ገበያና በኒው

Hawassa lost to Harer 2-0

Image
Hawassa, Ethiopia  – Harar Brewery scored the biggest upset of the week with a 2-0 victory over Hawassa City in Week 3 of the Ethiopia Premier League here today. Mugher Cement shared a point (0-0) on the road with newly promoted Arba Minch Kenema; EEPCO drew 2-2 with Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and Defence Force was held to a 1-1 tie with the visiting Sidama Coffee in Addis Ababa. So after today’s matches, Harar Brewery, Mugher Cement & EEPCO share the top spot with 5 points each, but with the Harari side having a better goal difference (+2 goals). The league will continue on Tuesday, December 13 with the following matches: Bishoftu: Air Force vs Dedebit FC Dire Dawa: Dire Dawa City vs St. George FC Addis Ababa: Ethiopian Coffee vs Adama City FC

Ethiopian Washed Coffee Prices Fall as Much as 6.9%

Prices for unwashed arabica coffee from  Ethiopia  fell as much as to 6.9 percent last week on the Ethiopia Commodity Exchange. Volumes of both washed and unwashed coffee traded rose to 2,529 metric tons in the week ending Dec. 9 from 2,295 tons a week earlier, according to e-mailed statement from the Addis Ababa-based exchange on Dec. 9. The following are prices for the most heavily traded types of arabica in dollars per pound on the last day they were exchanged in the week. Week-on-week data may reflect changes in exchange rates. Volumes are in metric tons and the percentage change is measured from the previous week’s closing price. Unwashed Region Type Grade Volume Price % Change Forest A 9 232.54 $1.9058 -0.14% Forest A UG 80.78 $1.9211 3.59% Forest B 7 45.9 $1.998 n/a Jimma A 8 30.02 $1.9672 1.45% Jimma B 6 45.9 $1.9

ቡና በብትን እንዲላክ የወጣው መመርያ ነጋዴዎችን አደናግጧል

Image
ከኅዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በንግድ ሚኒስቴር የወጣው መመርያ፣ ቡና በብትን በኮንቴይነር እንዲላክ የሚያሳስብ ነው፡፡ ቡናው በብትን መላኩ የሚያመጣው ጠቀሜታ ቢኖርም አነስተኛ ላኪዎችን፣ የቡና ደረጃዎችንና በይበልጥ ደግሞ የውጭ አገር የቡና ገዢዎችን ነባራዊ ሁኔታና ፍላጎት ከግምት ያላስገባ መሆኑን በመጥቀስ ነጋዴዎች ተችተውታል፡፡ አንዳንዶችም በአጠቃላይ የአገሪቱ የቡና ኤክስፖርት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳርፍ መሆኑን በመግለጽ መመርያው በቶሎ እንዲሻሻል ጠይቀዋል፡፡ ነጋዴዎች ከዚህ ቀደም በጆንያ እየሞሉ በኮንቴነር የሚልኩበት አሠራርን በብትን ኮንቴይነሩ ውስጥ በሚዘጋጅ የብትን ቡና መሙያ ከረጢት ተዘጋጅቶለት እንዲላክ በመመርያ መወሰኑ አንዳንድ ነጋዴዎችን አስደንግጧል፡፡ አንዳንዶችም በጆንያ የላኩት ቡና ከጂቡቲ ወደብ ተመላሽ እንደተደረገባቸው ለሪፖርተር የደረሱ ጥቆማዎች ያመለክታሉ፡፡ የቡና ጥራት መጓደል እንደ ጃፓን ያለውን ሰፊ ገበያ ካሳጣ በኋላ መንግሥት የተለያዩ ዕርምጃዎችን እየወሰደ ቆይቶ፣ ለጥራት ብቻ ሳይሆን ለቡና ደኅንነትና ለወጪ ቁጠባ ተገቢ ነው ያለውን የቡና አላላክ ዘዴን በመመርያ ለውጧል፡፡ ቡና በብትን ቢላክ ሊያስገኝ የሚችለውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በመተንተን የብትን ቡና አላላክን የሚያቀነቅኑት አቶ ግርማ ቡታ ናቸው፡፡ በአካካስ ሎጂስቲክስ ኩባንያ የኤክስፖርትና የመርከብ አገልግሎት ኃላፊ የሆኑት አቶ ግርማ፣ ምንም እንኳ በብትን ቡናን መላኩ በሌላው ዓለም የተለመደና ኢትዮጵያ እጅግ ኋላ የቀረችበት ቢሆንም፣ ንግድ ሚኒስቴር የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ሳያወያይ መመርያውን ማውጣቱ በተለይ በጆንያ መላክ ያለባቸውን ነጋዴዎች እንደሚጐዳቸው አስረድተዋል፡፡ በብትን መላክ ማለት በኮንቴይነር ውስጥ በሚዘጋጅ ትልቅ