Posts

Showing posts from September, 2011
Image
New

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ማርቆስ ተክሌ አምስት አባላት ያሉት ጃፓን የኢትዮጵያን ቡና እንድትገዛ የሚያግባባ የልዑካን ቡድኑ መርተው ከትናንት በስቲያ ጃፓን ገቡ፡፡

Image
የአሜሪካና የአውሮፓ ኢኮኖሚ ለሁለተኛ ጊዜ አዘቅት ውስጥ እየገባ መሆኑን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ የሆነው ቡና ገበያ እንዳያጣ መንግሥትና የቡና ነጋዴዎች አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን በመፈለግ ሥራ ላይ ተጠምደው ሰንብተዋል፡፡ አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎች እንዲሆኑ የተመረጡት ጃፓን፣ ቻይናና ሩሲያ ሲሆኑ፣ ለሥራ ጉዳይ አዲስ አበባ የቆዩት በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ማርቆስ ተክሌ፣ አምስት አባላት ያሉት የልዑካን ቡድኑ መርተው ከትናንት በስቲያ ጃፓን ገብተዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ አባላት  በጊዜያዊነት የወጣውን አዲስ ዕቅድ ማለትም የቡና ነጋዴዎች ከገበሬዎች ሰብስበው በምርት ገበያ በኩል ከሚቀርበው ቡና በተለየ ሁኔታ፣  በዩኒየኖችና  በኢንቨስተሮች የሚቀርበውን ቡና ጃፓን እንድትገዛ ለማግባባት ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው የቡና መጠን ውስጥ 20 በመቶ የሚሆነውን ትገዛ የነበረችው ጃፓን፣ በቡና ውስጥ ለጤና ጠንቅ የሆኑ ኬሚካሎችን አግኝቻለሁ በሚል ቡና ከኢትዮጵያ መግዛቷን በማቋረጧ ነው፡፡ የተቋረጠውን ግብይት ለማስጀመር ኢትዮጵያና ጃፓን ባለፉት ጊዜያት በጉዳዩ ላይ ሲወያዩ ቆይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ በያዘችው አቋም ጃፓን ኬሚካሉን ያገኘችው ከኢትዮጵያ ወደ አውሮፓ ከተላከ ቡና እንጂ፣ በቀጥታ ከኢትዮጵያ ወደ ጃፓን ከተላከ ቡና ውስጥ አይደለም፡፡ ኬሚካል ተገኘበት የተባለው ቡና ደግሞ በጉዞና በተለያዩ ምክንያቶች ጃፓን እስኪደርስ ድረስ ስምንት ወራት የቆየ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ልትጠየቅ አይገባም የሚል መከራከርያ ቀርቧል፡፡ ይሁንና ጃፓን የኢትዮጵያን ቡና መግዛት በማቋረጥ ከቡና ውስጥ አራት ዓይነት የኬሚካል ይዘቶችን ስትመረምር ቆይታለች፡፡ በአሁኑ ወቅት ሦስት ኬሚካሎችን በቡናው ውስጥ ባለማግ

ጃፓን ለሲዳማ ዞን የገንዘብ ድጋፍ ሰጠች

አዲስ አበባ, መስከረም 18 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - ጃፓን በኢትዮጵያ በሰብአዊ ደሕንነት ላይ ለሚካሔዱ ሁለት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል የ225 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ሰጠች፡፡ የገንዘብ ድጋፉን ለመስጠት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የጃፓን ኤምባሲ ከሲዳማ ዞን እና ሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ከተሰኝ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን በጃፓን በኩል የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሒሮዩኪ ኪሽኖ፣ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እንዲሁ የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ ናቸው፡፡ የጃፓን መንግስት ለሰብአዊ ድህነነት ስራዎች ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን ድጋፉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንደሚው አምባሳደሩ ጠቁመዋል ጃፓን ከ1997 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በትምህርት፣ በመጠጥ ውሃና በሌሎችም መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎትን በሚያሟሉ ዘርፎች ከ300 በላይ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጓን አብራርተዋል፡፡ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ እና የሪሰሬክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎመንት ዳይሬክተር አቶ በላቸው ለማ በዚሁ ወቅት የገንዘብ ድጋፉን በአግባቡ ለተፈቀደለት ስራ በማዋል ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡

በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጥ የነበረው የወርቅ ግዥ ሥርዓት በሐዋሳ መስጠት ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ, መስከረም 18 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጥ የነበረው የወርቅ ግዥ ሥርዓት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በክልል አራት ከተሞች አገልግሎት መሰጠት እንደሚጀመር የማዕድን ሚኒስትሯ አስታወቁ፡፡ የማዕድን ሚኒስትር ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአገር አቀፍ ደረጃ የወርቅ አቅርቦት መጠን እየጨመረ በመመጣቱ በብሔራዊ ባንክ ብቻ ይሰጠው የነበረውን ግዥ ወደ ምርት አካባቢዎች ማስፋት አስፈላጊ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴሩ ወርቅ ከሚመረትባቸው ክልሎች መካከል በሐዋሳ፣ በጅማ፣ በመቀሌና በአሶሳ በሚገኙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ግዥውን ሥርዓቱ ከሚቀጥለው ሳምንት በይፋ እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለብሔራዊ ባንክ የቀረበው የወርቅ መጠን ሰባት ቶን የነበረ ሲሆን፣ በያዝነው ዓመት ግን ምርትና አቅርቦቱ ከ13 ቶን በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል፡፡ በክልሎች የወርቅ ግዥ ጣቢዎች መክፈት ወርቅ አቅራቢዎች ወደ አዲስ አበባ ያደርጉት የነበረውን ረጅም ጉዞ ከማስቀረቱ ባሻገር፤ ፈጣንና ቀልጣፋ የግዥ ሂደት ለመፍጠር እንደሚያስችል ሚኒስትሯ አስረድተዋል፡፡ በተለይ ወርቅ አምራች የኅብረት ሥራ ማህበራት በአቅራቢያቸው ወርቅ የሚሸጡባቸው የግዥ ማዕከላት ባለመኖራቸው ለሌላ ገዢ በመሸጥ ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም ሳያገኙ መቆየታቸን ወይዘሮ ስንቅነሽ ገልጸዋል፡፡ በአራቱ ከተሞች የግዥ አገልግሎቱ ሲጀመር ግን የወርቅ አቅራቢዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ይሆናል ብለዋል፡፡ በክልል ከተሞች በሚካሄደው የወርቅ ግዥ ሥርዓት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በአዲስ አበባ ማዕከል የሚሰጡትን ዓይነት አገልግሎት እንደሚሰጡም ሚኒስትሯ አመልክተዋል፡፡ በነዚህ የግዥ ጣቢያዎች

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚመጡ ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ እንዲያሰለጥን ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት  የሚመጡ ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ ተቀብሎ እንዲያሰለጥን ተመረጠ።         ዩኒቨርሲቲው በሁለተኛ ዲግሪ ስልጠና ለመስጠት የተመረጠው ከዘጠኝ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተወዳድሮ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ነው። የዩኒቨርሲቲው ማርኬቲንግና ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መልሰው ደጀኔ ለኢ ዜ አ እንዳሉት ስልጠናው የሚሰጠው በ11 የተለያዩ ፕሮግራሞች ነው። ዩኒቨርሲቲው ስልጠናውን የሚሰጠው  በአውሮፓ ታዋቂ ከሆነው ኢራስመስ ከተባለው ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ፣ የካሪቢያንና የፓስፊክ ፕሮግራም ማዕቀፍ ጋር በመተባበር ነው።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለከተማው አዲስ ከንቲባ ሾመ

  አዋሳ, ነሐሴ 30 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በደቡብ ሕዝቦች ክልል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ተጀመረ፡፡ ምክር ቤቱ ጉባኤውን ሲጀምር ለሀዋሳ ከተማ ከንቲባነት በሙሉ ድምጽ የሾማቸው አቶ ዮናስ ዮሴፍ ቀደም ሲል የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ የነበሩ ናቸው። አዲሱ ከንቲባ ቀደም ሲልም በሲዳማ ዞን የዳሌ ወረዳ አስተዳዳሪ ፣የሲዳማ ዞን ትምህርት መምሪያ ሃላፊ በመሆን ያገለገሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ ሾመቱን የሰጠው ቀደም ሲል የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በነበሩት በአቶ ሽብቁ ማጋኔ ምትክ መሆኑም ተገልጿል፡፡ የከተማው ምክር ቤት ጉባኤ የ6ኛ መደበኛ ጉባኤውን ቃለ ጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ በሶስት ቀናት ቆይታው በ2003 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ፣በ2004 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡

በሀዋሳ ከተማ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ስራ አከናወኑ

አዋሳ, ነሐሴ 30 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በሀዋሳ ከተማ ለሁለት ወራት በተካሄደ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልገሎት ከሁለት ሚልዮን ብር የሚበልጥ ግምት ያለው ስራ መሰራቱን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ ገለጸ፡፡ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ሲካሄድ ምክትል መምሪያ ሃላፊው አቶ በላይ ዲካ እንደገለጹት በከተማው ስምንት ክፍለ ከተሞች 36 ሺህ 155 ወጣቶች ነፃ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከተሳተፉት ወጣቶች መካከል ስምንት ሺህ 903 ሴቶች መሆናቸውን ገልጸው ወጣቶቹ በማጠናከሪያ ትምህርት፣ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ችግኝ ተከላ፣ በጤና፣ በአረጋውያንና ወላጅ አልባ ህፃናት ድጋፍ ላይ ያበረከቱት አስተዋፅኦ 2 ሚልዮን 57 ሺህ 150 ብር መገመቱን አስታውቀዋል፡፡ ወጣቶቹ ከራሳቸውና ሌሎች ወገኖች አልባሳትና የፅህፈት መሳሪያ በማሰባሰብ ለ3 ሺህ 160 አረጋውያንና ወላጅ አልባ ህፃናት ከማከፋፈላቸው በተጨማሪ የስምንት አረጋውያንን መኖሪያ ቤት መጠገናቸውን ገልጸዋል፡፡ የደቡብ ክልል ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ ምክትል ሃላፊና የሴቶችና ህፃናት ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ህይወት ሃይሉ እንዳሉት ወጣቶቹ በእረፍት ጊዜያቸው ያበረከቱት አገልግሎት ለማህበረሰቡ ካስገኙት ጠቀሜታ በተጨማሪ የህይወት ክህሎት ትምህርት የቀሰሙበት ነበር፡፡ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ተወካይ አቶ ታዬ ቢሊሶ በከተማው እየተከናወነ ያለው የልማት ስራ ቀጣይ እንዲሆን ወጣቱ በበጎ ፈቃድ አገልገሎት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበው የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ተሳታፊ ለሆኑ ወጣቶችና ድጋፍ ላደረጉ መንግስታዊና መንግስ

Ethiopian diaspora in US to build trade center worth 127m Birr in Hawasa.

South Ethiopia Community members living in United States (US) are to build a trade center worth 127 million Birr in Hawasa town. Representatives of the Community members and government officials on Thursday held a panel discussion in ERTA studio on ways of advancing development participation for Ethiopian diaspora. On the discussions, South Ethiopia Community President in US, Abbas Hussien said members of the Community have finalized preparations to build the trade center in Hawasa town. He said the Community is receiving the necessary support from the government, in an organized activity about 200 members are undertaking to be part of the ongoing development endeavors at home. Government officials participated in the discussions stated efforts made by the government to boost development participation of Ethiopian diaspora.

How Hawassa is changing

New

በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን በትምህርት ልማት ዘርፍ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ የትምህርት ልማት ሰራዊቶች ተሸለሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን በትምህርት ልማት ዘርፍ  የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ከ100 በላይ የትምህርት ልማት ሰራዊቶች ተሸለሙ። በሃዋሳ ከተማ ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው አጠቃላይ የትምህርት ጉባኤ የላቀ ውጤት  ላስመዘገቡ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ትምህርት ቤቶችና የትምህርት ጽህፈት ቤቶች የማበረታቻ ሽልማት  በመስጠት ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል። ለተሸላሚዎቹም የዋንጫ፣ የሜዳሊያ የቦንድና የተለያዩ ቁሳቁሶችን በሽልማት ተሰጥቷል። የጉባኤው ተሳታፊዎች ባወጡት የአቋም መግለጫ መላውን ህብረተሰብ በላቀ ሁኔታ በማነቃቃት  የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትን በሙሉ ወደ ትምሀርት  ቤት ለማምጣት በግንባር ቀደምትነት ለመንቀሳቃስ ቃል መግባታቸውን ባልደረባችን ሰለሞን ገመዳ ከሃዋሳ ዘግቧል። 

የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 5 ፣ 2003 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አዲሱን  ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተለያየ የወንጀል ድርጊት  ተከሰው በፍርድ ማረሚያ ቤት ከቆዩ የህግ ታራሚዎች መካከል ይቅርታ የተደረገላቸው የባህሪ ለውጥ  ያመጡና የእስራት ጊዜያቸውን ያገባደዱ ናቸው ። የተደረገው ይቅርታ በሙስና ፣በአስገድዶ መድፈር፣ በዘር ማጥፋትና በግፍ በሰው ህይወት ማጥፋት ክስ  ተመስርቶባቸው የተፈረደባቸውን እንደማይመለክትም አስታውቀዋል። ይቅርታ የሚደረግላቸው ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀለቀሉ ዳግመኛ በወንጀል ድርጊት ባለመሳተፍ  የበደሉትን ህዝብና መንግሰት መካስ እንዳለባቸው ነው የሳሰቡት። ህብረተሰቡም ይቅርታ ለተደረገላቸው ታራሚዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።

በደቡብ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ሊሰጠን ይገባ የነበረውን የስራ ደረጃ ዕድገት አላገኘንም አሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ)  በደቡብ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች  አምና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ሊሰጠን ይገባ የነበረውን  የስራ ደረጃ ዕድገት አላገኘንም አሉ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ  ቢሮ ሀላፊ አቶ አቶ ደበበ አበራ በበኩላቸው ችግሩ መሰረታዊ የአሰራር ሂደት ተግባራዊ ሲደረግ የተከሰተ እንደሆነ ተናግረዋል። ሰራተኞቹ ለኤፍ ቢ ሲ ሪፖርተር እንደነገሩት ከደመወዝ ጭማሪው ጋር ተያይዞ በክልሉ የመሰረታዊ  የአሰራር ሂደት ለውጥ ተግባራዊ ቢደረግም ምደባው ችግር አለበት  ነው የሚሉት። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሀላፊ አቶ አቶ ደበበ አበራ በበኩላቸው  ችግሩ መሰረታዊ የአሰራር ሂደት ተግባራዊ ሲደረግ የተከሰተ እንደሆነ ተናግረዋል። በ15 ቀናት ውስጥ ቅሬታዎቹ ምላሽ እንደሚያገኙም ነው ያስታወቁት። በመላው ሀገራችን የሰራተኛውን ገቢና የኑሮ ውድነት ታሳቢ በማድረግ መንግስት  በ2003 አጋማሽ ላይ ለሁሉም የመንግስት ሰራተኛ የደመወዝ ጭማሪ አድርጓል። ይህም በሁሉም የመንግስት ሴክተር መሰሪያ ቤቶች ነው ተግባራዊ የተደረገው። ከዚህው ጋር በታያያዘም የሰራተኛው የደረጃ እድገት በአብዛኞቹ ክልሎች ተግባራዊ ተደርጓል። የደቡብ ክልል የመንግስት ሰራተኞች ቅሬታ አምና ተግባራዊ ከተደረገው የደመዎዝ ጭማሪ  ጋር በተያያዘ የስራ ደረጃ አመዳደብ ጋር ይያያዛል። ሰራተኞቹ የሚያነሷቸው ቅሬታም የስራ ደረጃ ዕድገቱ ፍትሃዊ አይደለም የሚል ነው።  ሰራተኞቹ አሉ የሚሏቸውን ችግሮች ያነሳሉ። በሌሎች ክልሎች ተግባራዊ መደረጉንም ያነሳሉ። ክልሉ አስቸኳይ መፍትሄ ይፈልግልን ነው የሚሉት። አቶ ደበበ አበራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳርና የቢሮው ሀላፊ ናቸው። በሀገር