በሲዳማ ዞን ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጠ

አዋሳ, ህዳር 26 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን በበጀት አመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ 25 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የዞኑ ንግድና ኢንደስትሪ መምሪያ ገለጸ።
በመምሪያው የኢንቨስትመንት የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለሀብቶቹ የሚሰማሩባቸው የስራ መስኮች በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለመሰማራት ነው።
በሩብ ዓመቱ ፈቃድ የወሰዱት ባለሀብቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት በሁለት ባስመዘገቡት ካፒታል በ30 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንደነበረው ገልጸው ባለሀብቶቹ 3 ሺህ ሄክታር መሬት በማግኘታቸው ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ሲገቡ ከ4 ሺህ 500 ለሚበልጡ ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል።
መምሪያው ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸው የተሰጣቸው ያላለሙና ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፈው የሰጡ 19 ባለሀብቶች የወሰዱትን ቦታ በመመለስ ፈቃዳችው እንዲሰረዝ ማድረጉን ጠቁመዋል።
በዞኑ ወርቅ ታንታለምና የማእድን ውሃና ለተለያየ አገልግሎት የሚውል ሰፊ መሬት እንደሚገኝ ጠቁመው በመስኩ መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች መምሪያው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር