የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው


አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት
ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው።
በሬዲዮ ጣቢያው አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ትናንት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የጋራ
ውይይት ተካሂዷል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት  የማህበረሰብ ኤፍ ኤም 
ሬዲዮ ጣቢያው ስርጭት ዓላማ የተቋሙን የመማር ማስተማር፣ የምርምርና
የህብረተሰብ አገልገሎት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ነው፡፡
ጣቢያው ለጊዜው በ50 ኪሎ ሜትር ዙሪያ አገልግሎቱን የሚጀመር ሲሆን ቀስ በቀስም 
የስርጭት አድማሱን እንደሚያስፋፋ ጠቁመዋል። 

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር