የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ


አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 5 ፣ 2003 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት አዲሱን
 ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ 5 ሺ 671 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተለያየ የወንጀል ድርጊት 
ተከሰው በፍርድ ማረሚያ ቤት ከቆዩ የህግ ታራሚዎች መካከል ይቅርታ የተደረገላቸው የባህሪ ለውጥ 
ያመጡና የእስራት ጊዜያቸውን ያገባደዱ ናቸው ።
የተደረገው ይቅርታ በሙስና ፣በአስገድዶ መድፈር፣ በዘር ማጥፋትና በግፍ በሰው ህይወት ማጥፋት ክስ 
ተመስርቶባቸው የተፈረደባቸውን እንደማይመለክትም አስታውቀዋል።
ይቅርታ የሚደረግላቸው ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀለቀሉ ዳግመኛ በወንጀል ድርጊት ባለመሳተፍ 
የበደሉትን ህዝብና መንግሰት መካስ እንዳለባቸው ነው የሳሰቡት።
ህብረተሰቡም ይቅርታ ለተደረገላቸው ታራሚዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር