በሃዋሳ ከተማ በግጭት አፈታትና ሰላም ላይ የሚመክር አህጉራዊ አውደ ጥናት ተጀመረ

ሃዋሳ, የካቲት 14 ቀን 2003 (ሃዋሳ) - በምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግስታት አባል ሀገሮች ኢጋድ ድንበር ተሻጋሪ አካባቢ በሚኖሩ ህብረተሰብ መካከል የግጭት አፈታትና ሰላም ላይ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ የተዘጋጀ አውደ ጥናት ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ተጀመረ ።

በኢጋድ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ ተቋም ከጀርመን መንግስት ጋር በመተባበር ለሦስት ቀናት በተዘጋጀ አውደ ጥናት ላይ ከኢትዮጵያ ፣ከኬኒያ ፣ ከሶማሌያ፣ከጅብቲ፣ከሱዳንና ኡጋንዳ ድንበር ተሻጋሪ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ተወካዮች መሳታፋቸውን የተቋሙ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር ሚስስ ትእግስት ሀይሉ ገልፀዋል ።

ተሳታፊዎቹ በቆይታቸው በግጭት አፈታት ፣በሠላም ፣በልማትና ሌሎች የጋራ ስምምነትና ጥቅሞች ላይ የየአካባቢያቸውን ምርጥ ተሞክሮ በተናጥልና በቡድን በማቅረብ የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል ።

የምርጥ ተሞክሮና የልምድ ልውውጥ መድረኩ በፊልምና በተዘጋጁ የሬዲዮ ድራማዎችና የእርስ በርስ ባህላዊ ግንኙነቶች ላይ በተደገፈ ፕሮግራም የሚካሄድ መሆኑን ገልጠዋል ።

አውደ ጥናቱን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው ።

በአውደ ጥናቱ ላይ የየሀገሪቱ መንግስታትና የመስተዳድር ተወካዮች አጋርና መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳተፈዋል ።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር